Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

የጦር ሜዳ ውሎዎች.pdf


  • word cloud

የጦር ሜዳ ውሎዎች.pdf
  • Extraction Summary

ቫሓኀቫዐ ከእስር ቤት መፈታትና ወደ ሲቪል ሕይህወት መሸጋገር ኀዓዓናኀዓ ተ ደ ዱዓ ቫኀ ተኀኀኀኀ ና ዳግም እስራት በእናት ሀገር ከዚያ ሁሉ በኋላ ሰዎች በሕይወታቸው ሳሉ የግል ታሪካቸውን ራሳቸው መጻፍ የጀመሩበትን ወይም በሕይወት እያሉም ሆነ ከሕልፈተ ሕይወታቸው በኋላ ሌሎች ሰዎች እየጻፉላቸው ለንባብ የበቃበትን ጊዜና ዘመን ወደ ኋላ ስመለከተው ብዙ ትዝታዎችን ጥሎልኝ አልፏል ደርግን የመሰለ ግዙፍ ሠራዊት ያለው ኃይል ከሥልጣኑ ወርዲዷል ይህ ለምን እንደሆነ ሲታይና ከወታደራዊ ሳይንስ አንጻር ጥልቀት ባለው መልኩ ሲተነተን የተለዩ ምክንያቶች ሊኖሩት ይችላሉ ዛሬ ተሸነፈ የምንለው ሃይል ትላንት ምን ነበር።

  • Cosine Similarity

አናንተ ቀስ ብላችሁ ወደ ኋላችሁ ተመለሱ» አልኳቸውና በመጀመሪያ ወደ አየነው ነብር አፈሙዜን ደገንኩ ነብሩ አፉን ከፍቶ ይመሰከተኛል ጓደኞቼ ወደ ኋላቸው ቀስ እያሉ መመለሳቸውን ከአረጋገጥኩ በኋላ እኔም ወደ ኋላዬ አፈግፍጌ ሸስሸሁ ይህንንና ይህንን የመሳሰሉ አጋጣሚዎች ዛሬ የማስታውሳቸው ለአደን ወደ ጫካ በምወጣበት ጊዜ የነበረው ውፃ ጥም ረዛብ ድካምና ለህይወት አደገኛ የሆኑ ሁኔታዎችን መቋቋም ባልችል ኖሮ ጥሩ አዳኝ ለመሆን ባልበቃሁ እንግዲህ ለእኔ እዚህ መድረስ መሠረት የሆኑት በልጅነቴ የነበረኝ የጫካ አደን አባቴ ስለ አርበኝነትና አገር ወዳድነት የነገሩኝና ያስተምሩኝ የነበረው ትምህርትና የመልካም ሥነምግባር መመሪያ ወደ መሣሪያ ፍቅርና ወደ ወታደርነት ህይወት እንድገባ አስተዋፅዖ አድርጓል ነገሌ ቦረና አፄ ካሌብ ትምህርት ቤት ኛ ክፍል እያለሁ ቦይ እስካውት ውስጥ ገባሁ ቦይ አስካውት በመግባቴ ተደሰትኩ እኔ ብቻ አልነበርኩም አባቴም በጣም ተደሰቴ ቀደም ሲል የተለማመድኩት የአግር ጉዞና የአደን እንቅስቃሴ በጣም ረዳኝ ወዲያውኑ የቴንደርፉት በእስካውት ትምህርትና ስልጠና የጀማሪዎች የእስካውት ሰልጣኞች አለቃ ሆንኩ በወቅቱ በነገሌ ከሚከበሩት በአላት ሚያዚያ ዛምሌ እና ጥቅምት ምንጊዜም የማልረሳቸው በዓላት ናቸው በእነዚህ ክብረበዓላት በነገሌ ቢያንስ አንድ ሻለቃ ጦር አንዲሁም የስካውት ቡድን ይሰለፋል ከእድሜ እአኩያዎቼ መካከል የቴንደርፋት የእስካውት ፃላፊ በመሆኔ በተለይ እኔን ልዩ ኩራትና ደስታ ያጎናዕፈኝ ነበር አንጋፋ የጦር መኮንኖችና አርበኞች በበዓሉ ላይ ሲስለፉ ቀደም ሲል ያገኙዋቸውን የጀግንነትን ድርጊቶች የሚያንፀባርቁ ሜዳሊያዎች ደረቶቻቸው ላይ ደርድረው ብቅ ይላሉ አኔ ደግሞ ያንን መሆን ያምረኛል የቀዳማዊ ኃይለሥላሴና በጀርባው ደግሞ የእቴጌ መነን ምስል ያለበት የቁልፍ ማንጠልጠያ አባቴን አስገዛሁና ጀግና አርበኛ ለመምሰል በመርፌ ቁልፍ ላይ ሰክቼ ደረቴ ላይ በመደርደር ሰልፍ አወጣለሁ በሰልፉ ላይ ይህንን አድራጎቴን ያዩ ሁሉ ግማሹ ሲስቅ ግማሹ ደግሞ ያደንቃል አሁን ወደ ኋላ ላይ ልብ አድርጌ ሳስበው ይህም ህይወቴን ወደ ውትድርናው ሙያ እንዳዘነብል ካደረጉት ምክንያቶች አንደኛው ሳይሆን አይቀርም የወጣትነት ዘመን የኛ ደረጃ ትምህርትና የይርጋ ዓለም ትዝታ በ ዓም የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንዳለፍኩ በ ዓም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን ለመቀጠል ወደ ጠቅላይ ግዛቱ ዋና ከተማ ወደ ይርጋዓለም ፄድኩ አዲስ ህይወት በአዲስ አካባቢ ጀመርኩ ይርጋዓለም ወይና ደጋ የሆነ ተወዳጅ የአየር ጠባይ ያላት የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ዋና ከተማ ነበረችፁ የተትረፈረፈ የቡና ሃብትና የቆጮ ተክል ያላት ኑሮ እጅግ በጣም ርካሽ የሆነባት ሀገር ናት ከወላጅና ከቤተሰብ ተነጥሎ አዲስ ህይወት መጀመር ቀላል አልነበረም በመጀመሪያ ከጓደኞቼ ጋር አዲስ ህይወት የመመስረቱ ጉዳይ ፃሳቤ ውስጥ ስንቅር ሲል ደስታ ቢጤ ይሰማኛል ከወላጅ መለየቱ ደግሞ ከባድ መስሎ ይታየኛል በእነዚህ ሁለት የፃሳብ ማዕበሎች ውስጥ እየዋዝቅሁ ነው ያቺን ውቧንና ለምለሟን ነገሌ ተሰናብቼ ወደ ይርጋዓለም ያቀናሁት በስንብቴ ዋዜማ የሽኝቱን መስተንግዶ በተመለከተ ሁሉም ነገር ተጠናቀቀ አንድ አገልግል ጭኮስሜታዊ ነበልባሉ የሚያቃጥል የወላጅ እናት እምባ የአባት ውጫዌ የቆራጥነት ስሜት ነገር ግን የአብራኩን ክፋይ እንዳው በቀላሉ መለየት ያልቻለ አንጀት እነዚህ ሁሉ በአንድ ምሽት ተሰናድተው በአንድ ኤንትሬ መኪና ወደ ይርጋለም ሸኘኝ የወላጅ አባቴን የመንፈስ ጥንካሬ ሁልጊዜ አደንቅላቸዋለሁ በዚያ ባረጀ የጭነት መኪና ተሳፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለያቸው ግን በቀላሉ ተሸነፉ አይናቸውን በዓይኔ ላይ ትክ አድርገው የመጨረሻውን የአባትነት ስንብት ከገለፁልኝ በኋላ ከመኪናው በስተጀርባ ፊታቸውን ዘወር አድርገው አለቀሰሱ ጉዞዋችንን ወደ ይርጋዓለም ቀጠልን ጊዜው የክረምቱ ዝናብ ያጨቀየው ምድር ስለነበረ ከተወሰነ ጉዞ በኋላ የምንጓዝበት የጭነት መኪና ከጭቃ ውስጥ ተዘፍቆ ወደ ጎኑ አዘነበለና ጋደልም አለፊ መኪናውን ጎትቶ ለማውጣት በጣም አስቸጋሪ ነው አካባቢውም በደን ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ስለነበር ከኋላችን የሚደርስልን ሌላ መኪና አልነበረም በዚያው ስፍራ አንድ ቀን አደርን መኪናው ወደ ጎኑ ሲፈነገል አገልግሉ ከውሃ ውስጥ በመግባቱ ለስንቃችን የተዘጋጀውም ጭኮ ውዛፃ ገባበትና ተበላሽ በሚቀጥለው ቀን አንድ መኪና ድንገት ከነጌሌ መጣ በዚያ መኪና ላይ ተሳፍረን ስንጓዝ ከዋልን በኋላ ዘንባባ ውፃ አደርን አሁንም ስንጓዝ ቆይተን በሶስተኛው ቀን ክብረ መንግስት ገባን ነገር ግን ምግብ ፍለጋ ወደ ከተማ መውጣት አስቸጋሪ ነበር አካባቢው ወርቅ የሚመረትበት ስለሆነ ወደ ከተማ የገባ ሰው ወርቅ በሆዱ ውስጥ በማስገባት ሰርቆ እንዳይወጣ በኤክስሬይ መፈተሽ ወይም እንግሊዝ ጨው አለያም ኮሶ መጠጣት አለበት ስለሚባል ፈራንና አንድ ቀን ጦማችንን አደርን ረሀቡም ተጨምሮ አዳራችንን ከባድ አደረገው በብርድ ልብሶቻችን ተጀቦንና እንደምንም ሌሊቷን አሳለፍን በማግሥቱ አውቶቡስ መጣልንና ጉዞ ቀጠልን ለመጀመሪያ ጊዜ አውቶቡስ ያየሁትም የተሳፈርኩትም ያን አለት ነበር ጉዞአችንን ከክብረ መንግሥት ቀጠልንና አለታወንዶ አዳር አደረግን አሁንም ከአለታወንዶ በፎርድ መኪና ተሳፍረን ከነገሌ በተነሳን በኛ ቀናችን ይርጋዓለም ገባን በመንገድ ላይ የገጠመኝ ውጣ ውረድ በቀላሉ ከቤተሰብ ተነጥሎ የራስን ሕይወት በደስታ ለመምራት ቀላል እንዳልሆነ የተገነዘብኩበት የመጀመሪያ አጋጣሜዬ ነው ማለት ይቻላል ከነገሌ ወጥቼ ይርጋዓለም ስገባ በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን ልዩነት ለማነጻጸር ሞክሬአለሁ ይርጋዓለም ከነገሌ ሻል ያለች ከተማ ናት ይርጋዓለም መብራትና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የነበሩባት መለስተኛ ከተማ ናት የወጣት ነገር ከሰ ራር ረ ፎሮ ር ሆኖ በተለይ የማልረሳው የሲኞር አልፊዩን ኬክ ቤት ነው በአልፊዩ ኬክ ቤት በአምስትና በአሥር ሳንቲም የሚሸጡ የተለያዩ ቅርጾች ያሉባቸው ኬኮች የነበሩ ሲሆን በተለይም በልብ ቅርፅ የተሠሩ ብስኩቶች አንዱ በ ሣንቲም በአራዳና በስደተኛ ሠፈር የተከፈለች ከተማ ናት አራዳ የከተማዋ ቆርቋሪ የሆኑት የራስ ደስታ ዳምጠው ቤተመንግሥትና ትቤቱ የሚገኙባቸው የንግድ ሠፈር ጭምር ስትሆን ስደተኛ ሰፈር ደግሞ የዱሮ ስደተኞች የኖሩበት ፍርድ ቤት ኬክ ቤቶችና በተለይም ደግሞ ከነገሌ ቦረና የሚመጡ ሰዎች የሚፈላለጉበት አካባቢ ስለነበረ የሰላምታ ደብዳቤ ለወላጆቼ ለመላክ በዕረፍት ጊዜዬ ስደተኛ ሠፈር አዘውትሬ እሄዳለሁ እንዲሁም ከአራዳ ስደተኛ ሠፈር ለመመላለስ አንድ ብስክሌት ገዛሁ በሕይወቴ አንድ ትልቅ ለውጥ አሳየ አራስን በራስ የመምራትና የተለማመድኩት ይርጋዓለም ነው ይህ ደግሞ የማስተዳደር ኃላፊነትን ለምግቤ ለቤት ኪራይና ለአንዳንድ ወጪዎች ወላጆቼ በወር መቶ ብር ይልኩልኛል ይህንንም ገንዘብ በተስተካከለ በጀት የመጠቀም ኃላፊነት ነበረብኝ መቶ ብር በዚያን ጊዜ ትልቅ ገንዘብ ነው አስፈላጊ ለሆኑ ነገሮች ተጠቅሜ ስለማልጨርሰው ጊዜ የተረፈኝን ገንዘብ ለአባቴ መልሼ የምሰጥበት ጊዜ አለ በጠዋት ተነስቶ እሳት አቀጣጥሎ ሻይ ማፍላት አልጋ ማንጠፍ ከባደኛቼ ጋር በቡድን ሆነን ማጥናት በአረፍት ጊዜ ቤተክርስቲያን መፄድ ፍልውሃ ፄዶ መታጠብ ይፄ ሁሉ ያለማንም አነሳሽነት በራሴ ግፊት በኘሮግራም የማከናውናቸው ተግባሮች ናቸው በዚያ ጊዜ ኃላፊነትን ወስጄ እራሴን የመምራቱ ሁኔታ አሁን ለደረስኩበት የዕድገት ደረጃ አስተዋፅዖው ከፍተኛ ይሸጣል ይርጋዓለም ለአረፍት ወላጆቼ ዘንድ በምሄድበት በወጣትነት ዘመን ነው የዛሬ ልጆች አብዛኛዎቹ ልጆቻችንን ጨምሮ መኖራቸውን ስመለከትና ከዱሮው ጋር ሳነፃዛፅር በጣም ይገርመኛል በክፍላችን ውስጥ ከነበሩት ተማሪዎች መካከል እኔ በዕድሜ አነስተኛ ነበርኩ ሁለት ሴቶች ልጆች ነበሩፎ ሴቶች ልጆች በትምህርት ቤት ውስጥ እንደብርቅ ይታያሉ በእድሜ አነስተኛ ር ስለሆንኩ አብሬያቸው አንድቀመጥ ተደረገጉ ያኔ በሴትና በወንድ ተማሪዎች መካከል የነበረው ግንኙነትና መተሳሰብ በቁም ነገር ላይ ነው ሌላው ቀርቶ በዚያ ጊዜ የነበሩትን የክፍል ጓደኞቼን ሳስታውስ እንዳሁኑ ጊዜ አንዳንድ ልጆች በተለያዩ ዕፆችና ሱሶች ተጠቂ መሆን ቀርቶ ሲጋራ እንኳን የሚያጨስ አንድም ተማሪ አልነበረም ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነገር ቢኖር መማርና ወደፊት ለታላቅ ቁምነገር ለመብቃት ጥረት የታከለበት ትግል ማካሄድ ብቻ ነው ግፋ ቢል ብስኩት እንገዛለን ሲሮኮና ስናኘ ኮላ እንጠጣለን የጓደኝነት ፍቅር በቀላሉ የሚታይ ስላልነበረ አብሮ መብላትና መተሳሰብን አናስቀድማለን ራስ ደስታ ዳምጠው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በጣም ጥሩ ትምህርት ቤት ነው ከፍተኛ የማስተማር ችሎታ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሕንዳዊያንና አሜሪካውያን የሰላም ጓዶች መምህራን ይገኙበታል መምህራኑ ከቀለም ትምህርቱ ባሻገር ወደ ፊት በሥራ ዓለም ስንሰማራ ትምህርቶችን ስላስተማሩን ባለውለታዎቻችን ናቸው በተማሪነት ሕይወቴ በትምህርት ቤት ውስጥ በአንዳንድ እንቅስቃሴዎች አሳተፋለሁ በግሌ በእግር ኳስ በእጅ ኳስ በቅርጫት ኳስ በሩጫና በከፍታ ዝላይ የስፖርት ዓይነቶች ብንቀሳቀስም ለትምህርት ቤቱ ቡድን የመሰለፍ አቅምም ሆነ ብቃት አልነበረኝም እነ አሥራት ገዳ ተስፋዬ ጋሻው አርጋው ከበደ ኤልያስ በቀለና ኤልያስ ኃይሉ ከክፍላችን ስመጥር ስፖርኞች ነበሩ ትዝ ይለኛልአሥረኛ ክፍል አያለን «ፊልድ ሰርቪስ» የሚባል ኘሮግራም መጣ ኘሮግራሙ አንድ ተማሪ በአሜሪካን አገር ለትምህርትና የሕብረተሰቡን ማህበራዊ ሕይወት ለማጥናት ለአንድ ዓመት የሚቆይበት ኘሮግራም ነው በትምህርት ቤታችን ለሕይወታችን ጠቃሚ የሆኑ ድ ከነበሩት አሜሪካውያን የሰላም ጓዶች መምህራን መካከል ይህንን ኘ ሮግራም የሚከታተሉት ሚስተር ክላርክ ነበሩ እድሉ ደግሞ የሚሰጠው ለአሥረኛ ክፍል ተማሪዎች ነበር እኔና ለማ መርዕድ በአሁኑ ጊዜ ዶክተር ከትምህርት ቤት ዕድሉ ተሰጠንና አንዳንድ ፎርማሊቲዎች እንድናሟላ ተደረገ በመጨረሻ ግን እኛ በማናውቀው መንገድ እድሉ ለአዲስ አበባ ልጆች ተሰጠና እኛም ሳንፄድ ቀረን እኔ በዚያን ወቅት የውጭውን ዓሰም ስለማላውቀው መቅረቴ ብዙም ስሜት አልሰጠኝም ሚስተር ክላርክ ግን በጣም አከኑ የዩኒቨርሲቲ መሰናዶ በልዑል በዕደማርያም ትቤት በ ዓም ኛ ክፍል ስደርስ ወደ ልዑል በዕደማርያም ትምህርት ቤት ለመግባት የሚሰጠውን ፈተና ወስጄ አለፍኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፋክልቲ ሥር የልዑል በዕደማርያም ላብራቶሪ ትቤት የሚባል አለ የዚህ ትምህርት ቤት ዋና ዓላማ በወቅቱ በአሥራ አራቱም ጠቅላይ ግዛቶች ከሚገኙ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከኛ ክፍል በአንደኞ ሰሚስተር ጥሩ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ፈተና በመስጠት በመግቢያ ፈተናው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ከዐዱ ተማሪዎችን መልምሎ አንድ ዓመት በኛ ክፍል ካስለጠነ በኋላ ወደ ትምህርት ፋኩልቲ በቀጥታ ማስገባትና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርነት ማስመረቅ ነው ለእረፍት ነጌሌ ወላጆቼ ጋ ስፄድ ያጋጠመኝን እድል አጫወትኳቸው በጣም ተደሰቱ ልዑል በዕደማርያም ትምህርት ቤት ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ስለነበረና አስተዳደሩም በዩኒቨርሲቲው ሥር ስለሆነ እዚያ ገብቶ መማሩ እንደ ታላቅ ነገር ስለሚቆጠር ወላጆቼ በጣም ተደሰቱ የእረፍት ጊዜዬን ወላጆቼ ጨጨ መ መ መመመ መ መ መ መ መ መመ ሥሩ ዘንድ አሳለፍኩና መስከረም ሲጠባ ከጓደኛዬ ጋር በጦር ሠራዊት መኪና ተሣፍረን አዲስ አባበ መጣን አዲስ አበባ ስመጣ ሁለተኛ ጊዜዬ ነበር ከመኪናው የወረድነው አራተኛ ክፍለ ጦር ስንደርስ ነው በመሺለኪያ መንገድ አራት አምስት የሚሆኑ አውቶሞቢሎች ተከታትለው ሲጓዙ በጣም ተገረምኩ ይርጋዓለም አልፎ አልፎ ብቅ ከሚሉት መኪናዎች ጋር ሳነጻጽረው አዲስ ነገር ሆነብኝ የመኪናው ብዛት እንደዛሬው እንደ አሸን የፈላበት ሁኔታ ቢሆን ኖሮ ይበልጥ በተደነቅሁ ነበር ጓደኛዬ ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ ፋሲል ሆቴል ወሰደኝና በዚያው አዳር ሆነ በማግሥቱ ኪሎ በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ቅጽር ግቢ ከሚገኘው ልዑል በእደ ማርያም ትምህርት ቤት ሪፖርት አደረግሁ የምዝገባውን ፎርማሊቲ ከአጠናቀቅሁ በኋላ መኝታ ተሰጠኝ ምግብ ቤቱንም አየሁ ብቻ አዲስ አበባን ብዙም ጠልቄ ስለማላውቃት ሁሉም ነገር አዲስ ሆነብኝና አስፈራኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ስገባ የግድ ሱፍ መለበስ አለበት የሚባል የውጭ ወሬ ስለነበረ ከሞዳኖቫ በመቶ ፃያ ብር ምን የመሰለ ሙሉ ልብስ ገዛሁ ተለዋጩን ደግሞ መርካቶ ከፔቲ ፖሪ ገዛሁና ከዳርማር ምርጥ የሆነ ጫማ በዛያ አራት ብር ሸምቼ ቂቅ አልኩ የዩኒቨርሲቲውን ተማሪ ወደ ውስጥ ገብቼ ሳየው ግን ጃኬትም ሹራብም አዘውትሮ ይለበሳል ያኔ ራንግለር ፒያሳ ከሳሙኤልና ከተውፊቅ ሱቆች በ ብር ይገዛል የሚያማምሩ የውጭ ሸሚዞች ዋጋቸው እርካሽ ነው እነሱንም ጭምር ገዛሁና አዲስ ሕይወት ጀመርኩ አዲስ አበባ ለአዲሱ ሕይወቴ አዲስ መሠረት ጀመረችልኝ የፊልም ወይም የሲኒማ ትርዒትን በተመለከተ ለየት ባለ መልኩ የቴክስ ፊልም ያየሁት አዲስ አበባ ነው ከዚያ በፊት ነገሌ ገበያው ላይ ሕዝብ በተሰበሰበበት ወይም በትምህርት ቤት ውስጥ በንጉሠ ወይም በሌላ ጉዳይ ላይ የሚያተኩሩ ትምህርታዊና ዘጋቢ ፊልሞችን ብቻ እንመለከት ነበር ሲኒማ አድዋ በሃምሳ ሣንቲም ቆንጆ ቆንጆ የቴክስና የፍቅር ፊልሞች ይታያሉ ሐሙስ ሐሙስ እኔና ጓደኛዬ ፈቃደ መርጊያ አሁን በሕይወት የለም ሲኒማ አድዋ እንፄዳለን አንድ ቀን ሁለታችንም በርት ላንካስተርና ኪርክ ዳግላስ አብረው የሰሩትን ፊልም አየን በሁለቱም የፊልም ተዋናዮች እንቅስቃሴ ተደነቅን ሁለታችንም ሁለቱን መሆን ፈለግን ስንወጣ አንተ በርትን እኔ ደግሞ ኪርክን እንሁን አልንና ተስማማን ወዲያውኑ እንደነሱ አካሄዳችንን ለወጥንና እግራችንን ሰናጥፍ ወጥረን ፒያሳን አቆራርጠን ሰባ ደረጃን ወጥተን በዕደ ማርያም ግቢ ደረስን የከተማ ልጅ የመሆኑን ኑሮ የጀመርኩት ከዚያ በኋላ ነበር ልዑል በእደማርያም ትምህርት ቤት ደስ ይላል ያስተዋወቀኝ ሌላው ነገር ቢኖር ሰፋ ያለ አዲስ ማህበራዊ ሕይወትን ነው ተማሪዎቹ ወደ ዐ የሚጠጉና ከአሥራ አራቱም ጠቅላይ ግዛት የተውጣጡ ምርጥና ብስል ተማሪዎች ነበሩ በብሔር በቋንቋ በባህል የተለያዩ ቢሆትም የሁሉም ዓላማ ትምህርትና የኢትዮጵያዊነትን መልክ የያዘ ነው በተለይም ደግሞ ሁላችንንም ይበልጥ የሚያስተሳስበን የምንኖረው በአራት ክፍሎች በተከፈሉ መኝታ ቤቶች ውስጥ ስለሆነ አብረን እንማራለን እናጠናለን እንመገባለን እንደ ዱሮው እንደ ይርጋዓለም ሶስት አራት ሆኖ ማደሩ ቀረና ፃምሳ ስልሳ የምንሆን ተማሪዎች በአንድ ክፍል ውስጥ ማደር ስንደምር ሕይወት አዲስ ማህበራዊ ኑሮን እያጣጣመች መጣች ትምህርት ቤቱ ጠበቅ ያለ የዲስኘሊን መመሪያዎች አሉት መመሪያ ደግሞ ለኔ ትርጉም አለው ይህ ደግሞ በቀጣዩ ወደ ሐረር ጦር አካዳሚ ስገባ የራሱን የሆነ የሕይወት ልምድ አስገኝቶልኛል ፌዴ መ በትምህርት ፋኩልቲ የዕጩ መኮንንነት ምልመላ የኛ ክፍል ትምህርቴን በልዑል በአደ ማርያም ትምህርት ቤት አጠናቅቄ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገባሁ ዩኒቨርሲቲ መግባት ደግሞ ራሱ በሕይወት ላይ ለውጥን ያስከትላል የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ደግሞ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተናን አልፈው ከመላው ሀገሪቱ የሚመጡ ናቸው ጥቅምት ወር ዓም ገደማ ይመስለኛል የኛ ዓመት ተማሪ እያለሁ በዩኒቨርሲቲው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ አንድ የስብሰባ ጥሪ ለኛ ዓመት ተማሪዎች ተላለፈ ቦታው ራስ መኮንን አዳራሽ ነው በጊዜ እራቱን በልቶ ወደ አዳራሹ የገባው ተማሪ መቀመጫ ይዛል መቀመጫ ያላገኘው የአዳራሹን ግራና ቀኝ ግድግዳ ተደግፎ ቆሟል ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሐረር ጦር አካዳሚ አዛዥ የነበሩት ሕንዳዊው ብርጋዴየር ጄኔራል ሻውንዳይል በአንድ ከፍተኛና በሶስት መስመራዊ መኮንኖች ታጅበው አዳራሹን መፃል ለመፃል ሰንጥቀው ወደ መድረኩ ብቅ አሉ ሁሉም የለበሱት የጦር ሠራዊት ዩኒፎርም ልዩ ግርማ ሞገስ አጎናጽፏቸዋል ዓይንና ልብን ያማልላል በተለይ የጄኔራሉና የኮሎኔል ብርሃኔ በሜዳልያዎች የተንቆጠቆጠ ደረት ምነው የጦር መኮንን ሆቼፄ ሁሉም ነገር በቀረብኝ ያሰኛል እንዳጋጣሚ ሆኖ ለዐኛ ኮርስ ከተመረጡት እጩ መኮንኖች በወቅቱ መስከረም ቀን ዓም ሪፖርት ያደረጉት ብቻ ስለነበሩ ኃይሉ አነስተኛ በመሆኑ ንጉሠ ነገሥቱን በማስፈቀድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፈቃደኛ የሆኑትን ለመመልመል መሰናዶ ተደረገ የዚያን እለቱ ስብሰባ የተጠራውም ለዚሁ ጉዳይ ነው በቅድሚያ ሕንዳዊው ጀኔራል ስለ ጦር አካዳሚው ሰፋ ያለ ንግግር አደረጉ ንግግራቸውን ቀጠሉ እያንዳንዱዋ ቃል በስሜትና በወታደራዊ ወኔ የተመላች ነበረች «ሞት እንደሆነ ለሁላችንም የማይቀር ነው ባንኮኒ ላይ ተደግፈህ ቡና ስትጠጣ ልትሞት ትችላለህ ከሁሉም ከሁሉም ግን ለሀገርና ለወገን መሞት ታላቅ ክብር ነው ቢያንስ ሁለት ዩኒፎርም መልበስም በራሱ ኩራት ነው አንድ የሲቪሉን አንድ ደግሞ የወታደሩን ማለቴ ነው ትምህርት እንደሆነ ከዚያም ስትመረቁ አያመልጣችሁም የኛ ፍላጐት ትምህርታችሁን እንድትቀጥሉና ምርጥ መኮንኖች እንድትሆኑ ነው አሉና አዳራሹን ከላይ እስከታች በንቁ አይኖቻቸው ቃኙት «እስቲ እዚህ ከተሰበሰባችሁት መካከል ከጦር አካዳሚያችን ተመርቃችሁ በዚህ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትምህርት የምትከታተሉ አጃችሁን አውጡ። ሩሩ የመሣሪያና የማስተማር ዘዴዎችን ያካተተ የንድፈዛሳብና የተግባር ትምህርቶች ተሰጡን በዚያን ጊዜ ማዕረጌ መቶ አለቃ ነበር ሥልጠናውን የምንካፈለው ለአሜሪካ የቅርብ ወዳጅ ከሆኑ ከአፍሪካ ከመካከለኛው ምሥራቅ ከአውሮፓ ከኤዥያና ከላቲን አሜሪካ ሀገሮች የተስባሰብን መኮንኖች ስንሆን በተለይ ደግሞ ከኢትዮጵያ የፄድነው ሠልጣኞች ኢትዮጵያዊነት ስሜት በጣም ይሰማን ነበር ሌላው ቢቀር በግብዣ ወቅት እንኳን አሜሪካኖቹ የሚሰጡንን ልብስ ሳይሆን የሀገራችንን ወታደራዊ ልብስ ለብሰን ነበር በቦታው የምንገኘው እነሱ የሚሰጡንን ልብስ የምንለብሰው በሥልጠናና በልምምድ ወቅት ላይ ብቻ ነው በምረቃ በዓላችንም ላይ የሀገራችንን ወታደራዊ ልብስ ለብሰን ነው የተገኘነው በዚያ ወቅት የነበረው የሀገር ፍቅር ስሜት ልዩና የሚያኮራ ሁኖ ነው ያገኘሁት ስለ ሀገራችን ክብር ስንል ከፍተኛ የሆነ ወታደራዊ ጨዋነትና ኢትዮጵያዊ ባህልን ለማሳየት የተቻለንን ጥረት ሁሉ አድርገናል ለኪስ ገንዘብ ተብላ በቀን የምትሰጠኝን አሥር የአሜሪካ ዶላር አብቃቅቼ ከአልባሌ ቦታዎች በመራቅ ራሴን የምጠብቅበት ሁኔታ ነበር በእርግጥም በዚያን ወቅት በጣም ይበቃኛል ኑሮም እስከዚህ ድረስ አስቸጋሪ አልነበረም በአሜሪካ ቆይታዬ በገጠሩም ሆነ በከተማው ጥሩ ኢትዮጵያዊያንንና አሜሪካውያን ጓደኞችን አፍርቻለሁ ጥሩ ጥሩ በጎና መጥፎ ሁኔታዎችንና አመለካከቶችን ተምሬአለሁ በነበርኩበት የኬንታኪ ክፍለ ሀገር ፎርት ኖክስ አካባቢ ሁለት ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ልጆች ነበሩ አንደኛዋ የሐረር ልጅ ስትሆን ሁለተኛዋ ደግሞ ኤርትራዊት ነበረች ሌላ ደግሞ ሉቪል ዩኒቨርሲቲ እንዳለች ብንሰማም ልናገኛት ግን አልቻልንም ከሁለቱ ጋር የተሳሰረ ግንኙነት ስለነበረን በበዓል ጊዜ እንጀራ የምንበላው ከአነሱ ጋር ነው ለበዓል ሁሉን ነገር ያመጡልናል ከመኖሪያ ቤታችን ባያገኙን እንኳን ከበራችን ላይ ያመጡልንን ምግብ ትተውልን ይሄዱ ነበር እንደቤተሰብ እንተያያለን ሁለቱ ባለትዳሮች ሲሆኑ በሁላችንም ዘንድ ያለው ኢትዮጵያዊ ስሜትና መከባበር አሁን ድረስ ትዝታው ይታወሰኛል በዚያን ወቅት ዘር ጎሳ ዛይማኖት የሚባል ነገር የለም በመጨረሻ ሥልጠናውን ወደ መጨረሱ ስንዳረስ አሜሪካኖቹ እናንተ በንጉሱ ጊዜ ስለመጣችሁ አሁን መሄድ የለባችሁም ፎርትኖክስ ከምኖርበት ቤት አካባቢ ከ ቅሩ ምንም የሚያጋጥማችሁ ችግር የለም ከፈለጋችሁ በርሲቲ አስገብተን ልናስተምራችሁ እንችላለን አለዚያም በዚሁ ዱሩ እ የሱማሌ ኃይል ንዑሳን ጣቢያዎችን በሚያጠቃበት ወቅት መደበኛው የወገን ሠራዊት ካለበት ቦታ እየተንቀሳቀስ መዋደቅ ጀመረ ምንም እንኳን በአካባቢው የነበረው የጦሩ ኃይል እጀግ አነስተኛ ቢሆንም የመጣውን የሶማሌ ኃይል አይቀጡ ቅጣት ቀጣው የኛ ኃይል ከሶማሌ ኃይል ጋር ሲነፃፀር አንድ ለስምንት ይሆናል የሱማሌ ዛይል በጎዴና በደጋዛቡር በኩል የማጥቃት ዛይሉን ሰነዘረ በፊቅ በኩልም የነበሩ ንኩስ ጣቢያዎች ስለተደመሰሱ ሌላ ተነጣይ ጦር መውጣት ስለነበረበት እኔ ቀድሞ የነበርኩበት ኛ ሜካናይዝድ ሻምበል ከኛ ብርጌድ መሃንዲስና ከቃኝ የተውጣጣ አነስተኛ ኃይል ፊቅ ዘምተው ፊቅ ላይ የተደመሰሰውን የፖሊስ ኃይል ተክተው መከላከል አደረጉ ፊቅ አካባቢ ያለው የጠላት ኃይል ቀላል አልነበረም ለመጀመሪያ ጊዜ የጥይት ጩኸት ከኢላማ ወረዳ ውጪ በውጊያ ግንባር የስማሁበት ወቅት ያን ጊዜ ነው ለዚህ ግዳጅ ቀለብ እንድናደርስ ትዕዛዝ ተሰጠ እኔ አንድ የመቶ ጦርና ሁለት ቃ ጂፖች በመያዝ ቅልፊቱን አጅቤ ባቢሌ ላይ ከሐረር ከመጣው አንድ በእግረኛነት ከተሰለፈው መድፈኛ ሻምበል ጦር ጋር ተገናኝተን አጅበን እንድንሄድ ተደረገ ነዳጅ ጥይትና ቀለብ ለጦሩ ይዘን መዓዝ ጀመርን በዚህ ቅልፍት ላይ ጠላት ጥቃት እንደሚያደርስበት ዛቻ መተላለፉ ቀደም ሲል ለኛ ብርጌድ መምሪያ መረጃ ደርሷል ሶማሌ «ቅልፊት ወይም ሞት» የሚል መፈክር አንግባ ተንቀሳቀሰች እኔ የምመራው ጦር ከዘጠነኛ ሻለቃ የተመደበልኝን አንድ የመቶ ጦር ሲሆን ቁጥሩ ከ አይበልጥምፁ በሁለት ቃፒ ጅፖች የሰው ኃይል አለ የሱማሌ ዛይል ሊሰነዝር የሚችለውን ጥቃት ለማምከን በጥንቃቂ ሸበሌን ዳካታን በሚገባ አሰስንና ባቢሌ ላይ የመድፈኛውን ኃይል ከሚመሩት ከሻምበል ተሾመ ተሰማ መ ሽሻ በምፅዋ ጦርነት ራሳቸውን በጀግንነት የሰው ጄኔራል መኮንን ጋር ተገናኝተን ጉዞአችንን ወደፊት ቀጠልን ከዚህም በተጨማሪ ሁለት ተጠርጣሪ ቦታዎችን በሚገባ ያሰስን ቢሆንም ምንም አላጋጠመንም ፊቅ ለመድረስ ኪሎ ሜትር ሲቀረን ምሽቱ እየተቃረበ መጣ ቅልፍቱ በሶማሌ ጦር የተዛተበት በመሆኑ ከአሁን በኋላ ወደፊት መግፋቱ አደገኛ ስለሆነ ባለንበት አካባቢ አዳር ማድረግ ተመራጭ መሆኑን ለቅልፍቱ መሪ አስረዳኋቸው እርሳቸው ግን እኔ ባቀረብኩት ሐሳብ አልተስማሙም ጉዞአችንን እንደቀጠልን ደቂቃ ሳይሞላ አንደኛውን ጀምስ መኪና ፈንጂ መታው ደግነቱ ቀለብ የያዘ ስለነበረ በሰው ላይ ጉዳት አልደረሰም ወዲያውኑ አስከትሎ የሶማሌ ወንበዴ የጥይት ናዳ አዘነበብን እኔ ከፊት የነበርኩ ሲሆን የቅልፍቱ አዛዥ ደግሞ ከኋላ ነበሩ በደመነፍስ ከነበርኩበት መኪና ተወርውሬ «ሳንጃ ባፈሙዝ። የበላይነትን ያስመዘግቡ ነበር የሶማሌ ሚግ የወደቀው ቶጎ ውጫሌ አካባቢ ስለነበር የእኛ የአየር ኃይል መውደቁን ለማረጋገጥ ተዚዙሮ ከተመለከተው በኋላ ጥሎት ሄደ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሶማሌ ሚግ ጥቃት ለማድረስ በእኛ ሠራዊት ላይ ዝቅ ብሎ አንዣበበ ካሊበር አሻቅበን ስንለቅበት በርግጎ ሜፄዶ ከካራማራ ሰንሰለት ላይ ልዩ ስፍራው ጉራች ከተባለ ተራራ ጋር ሄዶ ተላተመ ትዝ ይለኛል የእኛ ሰዎች የሞተውን አውሮኘላን አብራራ ሄደው ሲያዩት ቱታው ላይ ሁሴን የሜል ስም እንደነበረው መረጃ አግኝተናል ቦታ ይዘን እናድራለን የሶማሊያ ሚግ አውሮኘላኖች ጥቃት የማድረሳቸውን ተልዕኮ ለመቀጠል አንድ ቀን ይንቀሳቀሳሉ ጅጅጋን ያልፉና ካራማራ ላይ ታጥፈው በጅጅጋ አውርኘላን ማረፊያ ላይ ሲያንዣብቡ የአኛ ዐር ሚሊሽያ በማውረድ ላይ እያለ ተኩስ ከፈቱበት የእኛዎቹ አየር ኃይሎች ለካስ ገና ከፃርጌሳ ሲነሱ ይከታተሉዋቸው ስለነበረ በጭንዛፃቅስን በኩል አቋርጠው ይከቡዋቸዋል ሰማዩ ንፁህ ስለነበረ እኛም በርቀት አንመለከታቸዋለን ከሶማሌ ሚግ አውሮኘላኖች አንደኛው ገና የእኛን አውሮኘላኖች ሲያይ ፈረጠጠ ሁለተኛውን ከበው አዋከቡት የእኛ ሾኢ ተኩሱን ለቀቀው ቡልቅ ያለ ጭስ ታየ የሶማሌ ሚግ በአንድ ጊዜ ተቀጣጠለና ጭሱ እየበዛ ቀስ ብሎ ወደ መሬት ወደቀ በዚህ አይነት ዋነኛው ውጊያ ከመጀመሩ በፊት በነበረው የሶማሌ መንግሥት ጦር ትንኮሳ የእኛ ጦር የአየር የበላይነትን አሳየ የጠላት ጄት አንድ ቀን አሮሬሳ ላይ በነበሩት የእኛ ታንኮች ላይ ሮኬት ለቀቀብን ታንኮቻችንን ለመምታት ታስቦ የተደረገ ጥቃት ነው ግን አላገኙዋቸውም በአካባቢው የነበረውን ቁልቋል ደብድቦ ፈረጠጠ ሶማሌዎቹ ብቃት ያለው የጦር ልምምድ የላቸውም ከዚህም ባሻገር የአየር መቃወሚያ ይመታናል የሚል ፍራቻ አላቸው ብቻ ዝም ብለው አንዣበው ዝም ብለው ይፈረጥጣሉ ይህ ደግሞ ለአኛ ማንነታቸውን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል ስለዚህ የእኛ አየር ኃይል ደግሞ ስልቱን እየቀያየረ ያጠቃቸዋል እያደር ማንነታቸውን ሲረዳ መሬት ድረስ ዝቅ ብሎ መደብደብ ጀመረ አየር መቃወሚያዎችንም እያነጣጠረ ማጥፋት ቀጠለ የእኛንና የእነሱን አየር ኃይል ብቃት በቀላሉ መገመትና ማነፃፀር ይቻላል ተ በዚህ ሁኔታ ላይ እያለን በነፃሴ ወር ለማ ደጋ ያለ ምድብ ሌተና ኮሎኔል አሰፋ በነበሩበት የጦር ግንባር ፊትለፊት ጠላት ማታ ማታ ኃይሉን ወደ ወገን ይዞታ ማስጠጋት ጀመረ በዚህ ጊዜ ብርጌዱ በቅኝት መልክ አንድ ታንከኛ የመቶና አንድ እግረኛ የመቶ ወደፊት እንዲወጣ አዘዘ ቢቻልም በአውርኘላን እንመታዋለን የሚል ትዕዛዝ ደረሰንና አሰሳ ሲያደርጉ የሶማሌ ጦር እግረኛውን ከፊት አስቀድሞ ከኋላ ብረት ለበስ አስከትሎ ሣር ውስጥ ተሰግስጎ አገኙት እዚያ ቦታ ላይ በወገንና በጠላት መካከል ከባድ ተኩስ ተከፈተፅ ኤምዐ ታንክ ጥሩ መሣሪያ ነው በዚህ መሣሪያ ሲያጣድፉአቸው አንደኛው የሶማሌ ብረት ለበስ ወዲያው ተመታ የወገን የመቶ እግረኛ ጦር ወዲያው ወረደና የጨበጣ ውጊያ ጀመረ የሶማሌ ጦር ሣሩን ተከልለው ፀረ ታንክ አርፒጂ በታንኩ ላይ ተኮሱ ኮሎኔል አሰፋ ከታንኩ በስተጀርባ በቃሺ ጂኘ ይከተሉ ነበር ታንኩ ፀረ ታንክ ሲተኮስበት ወደኋላ ወጣ ብሉ አቅጣጫ መቀየር ነበረበት አለበለዚያ ግን በቀጥታ ኢላማ ሊሆን ይችላል ጂኾ ግን ታንኩን ተከትሎ ሥሩ ላይ ስለነበረ ሌኮሎኔሉ በታንኩ ግጭት ምክንያት ህይወታቸው አለፈ ሌተና ኮሎኔል አሰፋ ረጋ ያሉ ቆራጥ ንን ልየ ያላቸው አስተዋይ ቀልደኛና መልካም ራፅይ ያላቸው መኮንን ነበሩ በኮሎኔል አሰፋ መሰዋት የወታደሩ ስሜት ገነፈለና በቆራጥነት በውጊያው ውስጥ ገብቶ ጠላትን እንዳለ ጨፈጨፈው የጠላትን ጥይትና መሣሪያ ማረከ ከኋላ የነበረውም የጠላት ጦር እንደለመደው አግሬ አውጭኝ ብሎ ፈረጠጠ ከእኛ ወሽ የተሰውት የዘመቻ መኮንኑ የመአ ፀሐይ ዮሃንስ የሚባሉ ወጣት ቆራጥ የአካዳሚ ምሩቅ መኮንንና ወታደሮች ብቻ ናቸው ቁስለኛ እንኳን አልነበረም ርን ንእን ስ በዚያ የጦር ግንባር የነበረው ድል ለእኛ ወገን እንደ አይን መክፈቻ ሆነ ከዚህ በኋላ ነበር የጠላት ግፊት እያየለ የመጣብን በመቶ አለቃ ሳህለ ድንግል ብርፃኔ የሚመራ የኤምቭ ታንክ ሻምበል ከጅጅጋ ጥበቃ ተላቆ በስተግራ በኩል ስቡልቡሮል የሚባለውን ጋራ እንዲቆጣጠር ተደረገ ጀግናው አየር ኃይላችንም ቀን ቀን የተለመደ የቅኝት ተግባሩን ቀጠለ እኛም አካባቢውን ማታ ማታ እንቃኛለን በዚያ ዓይነት ሁኔታ የመከላከል ተግባራችንን ስናጠናክር ጉቤር ጫካ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የገባውን ታንከኛና መድፈኛ የኛ አየር ኃይሎች ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀሩ አደባዩት ነገር ግን አኛ ወደፊት ገፍተን ጥቃት እንድናደርግ ከመንግስት በኩል አይፈቀድልንም የእኛ ወገን ጠብ አጫሪና ተንኳሽ ሆኖ እንዳይገኝ መንግስት ይጠነቀቅ ነበር ሶማሌዎች ኃይላቸውን አጠናክረው ወደ ፊት ገፉ የእኛም ኢ አውሮኘላኖች በክልላችን ሶስት አራት ሆነው ቀኑን ሙሉ ይቃኛሉ ድንበራችንን አልፎ የመጣውንም የጠላት ኃይል ያጋዩት ነበር ከከቡልቡሮል ግራ በሶማሌ ይዞታ በኩል እየገሰገሰ በመሄድ ላይ ያለው የጠላት ጦር በቀጥታ በቅልፊት መልክ ከተፈሪ በር ማዶ አድርጎ ወደ ድሬዳዋ አቅጣጫ ተጓዘ ይህንንም አእንዳረጋገጥን የአውሮኘላን ድብደባ እንዲካሄድ ለበላይ አሳወቅን ነገር ግን የጠላት ጦር ወደ እኛ ግዛት የሚገሰግሰው የራሱን ግዛት ታኮ ስለነበር የእኛ መንግስት ደግሞ አርምጃ ለመውሰድ ያልፈለገው ጠብአጫሪ ላለመባል ነው ገረመን በአካባቢው የነበርነው ኃይሎች ደግሞ የጠላት ጦር እንደ አሸን እየተርመሰመሰ ወደ ግዛታችን ለመግባት ሲገሰግስ እናየዋለን በዚያን ወቅት የእኛ ኃይል ተገቢውን ጥቃት ቢያደርግ ኖሮ የጠላትን ፃይል ባለበት ቦታ ማሽመድመድና ቀጣይ እንቅስቃሴውን መግታት በተቻለ ነበር ጦርነት እስከተካሄደ ድረስ ከ መጃ ረ ሮርርጮር ዷ ን ንሲቪቲ እ መሆን የነበረበትም ይፄው ነወ ምክንያቱም ጠላት ጠላት ነውና ጠላት ከእኛ ግዛት ኦጋዴን ውስጥ ገብቷል እኛ ደግሞ በተለያዩ አቅጣጫዎች ሲዘምትብን መከላከል ነበረብን ግን አልሆነም የአመራሩ አንደኛውና ዋናው ድክመትም ይሄ ነው የጠላት አየር ኃይል በእኛ ላይ እንደልቡ በመብረር ቅኝትና አደጋ ሲያደርስ እኛ ም የዘወትር ሪፖርት ለበላይ ከማስተላለፍ አልቦዘንም ለካ የጠላት ዋነኛ ዓላማ ድሬዳዋን ለመምታት ስለሆነ ያሰበው ሁሉ ተሳካለትና ያ የተግበሰበሰ የጠላት ጦር ድሬዳዋ ደርሶ ውጊያ ተከፈተ የሠራዊቱ ሞራል ለጊዜው «የተነካ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ድሬዳዋ የነበረው ጦር ነበልባልና ህዝቡም ጭምር ከፍተኛ መስዋዕትነትን ከፍለው አውሮኘላን ማረፊያ ድረስ ገብቶ የነበረውን» የሶማሌ ኃይል ድባቅ መትተው ከአካባቢው ጠራርገው አባረሩት የእኛ አየር ኃይልም ተከታትሎ ወዶ አይሻ በኩል በማፈግፈግ ላይ የነበረውን የጠላት ኃይል እየደበደበ ወደ መጣበት አሳደደው ያ ለጊዜው ትንሽ ፋታ ሰጠ ነሐሴ ቀን ዓም ከነበርንበት ኪ ሜትር ገደማ ስንቅ ነዳጅና ጥይት አሟልቼ ጅጅጋ እንድመጣ በተሰጠኝ ትዕዛዝ መሠረት ጅጅጋ ሄድኩ ለሠራዊቱ የሚያስፈልገውን ስንቅና ትጥቅ ጭነን ነዳጅም በቦቴ ሞልተን በጥዋት ተመልሰን ወደ ጦር ግንባር ለመፄድ ስንዘጋጅ ከምሽቱ ሰዓት ገደማ ላይ በአሮፊሳ ግንባር ላይ የጠላት ጦር ውጊያ ከፈተ በዚያን ወቅት የእኛ ጦር ቀን ቀን የሚያሳልፈው ጋራ ላይ ሲሆን ማታ ማታ ደግሞ ከጋራው ላይ ወርዶ ሜዳው ላይ ነው እነርሱ ግን የእኛ ኃይል ጧትም ሆነ ማታ የሚውለውም ሆነ የሚያድረው ጋራው ላይ ስለመሰላቸው ባለ መድፍ የታጠቀ የጠላት ጦር የተኩስ ዝግጅቱን በጋራው ላይ ከፈተ የእኛ ጦር ግን ፀጥ ብሎ በንቃት ተዘጋጀ ጥዋት ማለዳ የሶማሌ ኃይል የጎህ ጥቃት ከፈተ ጥቃቱ በታንክና በብረትለበስ የታጀበ ፈርሙ ር መሚ ዓመ ትር እ ስለነበር ውጊያው እንደተከፈተ የእኛ ልጆች በኤም ፅዐ ታንክና በሻምበል መለስ ወዮሃንስ የሚመራው በጂፕ ላይ የተጠመደ ፋው ሚሳይል ትልቅ አስተዋፅኦ አድርጓል የቶው ሚሳይል ጥይት በወቅቱ እጅግ አነስተኛ ነበር ይህ የሆነው ከአሜሪካ መንግሥት ጋር የነበረው ግንኙነት በመቋረጡና ቀጣይ እደላው በመገታቱ ነበር እንጂ በርከት ያለ ክምችት ቢኖር ሁኔታዎች የተሻለ መልክ ይይዙ ነበር ያም ሆነ ይህ ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ሙሉ ሜካናይዝድ ብርጌዳቸውን ከጥቅም ውጪ በማድረግና በመማረክ ውጊያው በድል ተጠናቀቀ እኛ ደግሞ ከጅጅጋ ወደ ሃሮሬሳ ግንባር ለመንቀሳቀስ ስንጀምር እዚያ አካባቢ ያለው ሁኔታ ን መማ አዛዝ እንዳይነቃነቁ የሚል ትዕዛዝ አስተላለፉልን በ ተ ለ ጦር ሠፈር በጥገና ላይ የነበሩትን አንድ ሜካናይዝድ የሶማሊያ ብርጌድ ኃይሉን አጠናክሮ ሃሮሬሳን ለመያዝ ሙከራ ቢያደርግም የኛ ሠራዊት የመጣውን ጦር ድል አድርጎ ድምጥማጡን አጠፋው በለፌኤሳ በኩል ምንም ኃይል ስላለነበረን ሌላ አንድ የሶማሌ ሜካናይዝድ ብርጌድ እየገሰገስ ርን በለማ ደጋ በኩል ያለውንም የ «ለ» ምድብ በምሽት ውጊያ ር እንደገና በደገዘቡር መንገድ በስተቀኝ ማንም ያላየው ተን መጣበን ጅጅጋ ካለው የጦር ሰፈር ለመድረስ ንን ው እናይ ነበር ጦር ሰፈር ውስጥ ያሉትን ታንኮች ን ቦታ ቦታ ይዘን መከላከል ስንጀምር ኮሎኔል ኃይሌ ግንባር ያለው «ሀ» ምድብ ሠራዊት እንዳለ ተነቃንቆ ጅጅጋን እንዲከላከል ትዕዛዝ ሰጡ ሠራዊቱም በቅፅበት ወደ ጅጅጋ ተመለሰ በመቶ አለቃ ሳህለ ድንግል የሚመራው የኤም ታንክ ሻምበል በቶጎ ውጫሌ መንገድ «ሀ» ምድብ ደግሞ በለፌኤሳ መንገድ የመከላከያ ቦታ እንዲይዙ ተደረገ እኔ ሥመ መ መመመ ግሽ በደገዛቡር መንገድ በኩል ያለውን ሠራዊት ቦታ ሳስይዝ «ለ» ምድብ ተቀላቀለን በዚያ አቅጣጫ ከመጡት የጠላት ታንኮች ቱን ወዲያው ደመሰስናቸው የተቀሩት ወደ ኋላ አፈግፍገው ቦታ ያበ «ሀ» ምድብ በለፌኤሳ በኩል የመጣውን የጠላት ኃይል በሙሉ አቆመው ሳህለ ድንግል እልህም ንዴትም ይዞት ስለነበር በጠላት ታንኮች ላይ የጨበጣ ውጊያ ለማድረግ ሲዘጋጅ የነበረበት ታንክ ድንገት ተመታና ስሀገሩ በክብር ተሰዋ የመቶ አለቃ ሳህለ ድንግል ብርሃኔ ደፋር ሀገሩን የሚወድ ከሰው ጋር በአጭር ጊዜ የሚግባባ ለቤተሰቡ ከፍተኛ ፍቅር ያለው ሁላችንም የምንወደው ተስፋ የተጣለበት ቆፍጣናና ኩሩ ውድ የኢትዮጵያ ልጅ ነበር ነሀሴ ቀን ጅጅጋ ሊገባ የነበረውን የጠላት ኃይል በዚህ መልኩ አቀቆምነው የተረፉትን ታንኮችና ብረት ለበሶች በምሽት ጠጋግነን ተዘጋጀን ኤም ታንካችን የሚሠራው በቤንዚን ስለነበረ በጣም ተጎዳብን በዚህ ሁኔታ ላይ እያለን ጠላት ዛይሉን እያስባሰበና እያስጠጋ መጣ በደገዛቡርና በኦጋዴን የነበረውን ውርጅብኝ አወረደብን በተለይም ኃይሉን እያስጠጋ ከባድ የመድፍ በጦር ሠፈራችን በር ምሽግ አጠገብ ሆጌ ስመለከት የጠላት የፊት አስተኳሾች በሁለት ሺህ ሜትር ርቀት ባለው ድንጋያማ ቋጥኝ ውስጥ ሆነው የርቀት መመልከቻ መነፅራቸውን ጠምደው ለካስ የጦር ሰፈራችንን የሚያስመቱት እነሱ ናቸው ወንድሙ የሚባል በኋላ ምፅዋ ላይ የተሰዋ ጎበዝ ወታደር ነበር የብረት ለበስ ሹፌርነትንም የተካነ ሁለገብ ሰው ነበር ብረት ለበሱ ተጠግኖ አልቆ እንደሆነ ከጋራዥ አምጣልኝ» አልኩት ሮጦ አመጣልኝ አንድ ተጠግኖ የወጣ ኤም ታንክን ደግሞ በሩ ላይ ። የሚርመሰመሰውን የጠላት መኪና ታንክና መድፍ ይቀጠቅጣል አራት ተዋጊ ጀቶችና አንድ ካምቤራ ቦምብ ጣይ እየተፈራረቁ የጠላትን ኃይል ያጋዩታል በሩቅ ለተመለከተው እርሻ ውስጥ የተቃጠለ ክምር ይመስላል በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ አጥቂነት ስለተሸጋገርን ወድቆ የነበረው ሞራላችን በአንድ ጊዜ ታደሰ ይህንን ውጤት ለማየት መቻላችን ደግሞ የልብ ልብ ሰጠን በዚያን ጊዜ ከታንኩ ላይ እንደወረድኩ ጨበጣ ዉጊያ ውስጥ ገባን ከፅቱ ታንኮች አንደኛው ያልተመታውና ጭስ ከልሎት የነበረው የእግረኛው ኃይል ጨበጣ በመሰንዘር ሳይ መሆኑን ሲያውቅ ተደናጦ ሸበሸ በዚህ ወቅት ሰለሞን የተባለ የኛ ሻለቃ ባልደረባ ወታደር ኤም ሎው ፀረታንክ ተወንጫፊ ሮኬት መሣሪያ ይኮ ነበር ይቺን መሣሪያ ቀደም ሲል ብዙ ጊዜ ያስተማርኩባትና የማውቃት መሣሪያ ስለሆነች ከሰለሞን ላይ ተቀበልኩና በመሸሽ ላይ የነበረውን ታንክ ከኋላ በኩል መታሁት ታንኩም እየተቀጣጠለ ወደ ኛ ሻለቃ የቤተሰብ መኖሪያ ወደ አፈሩ ቤት አቅጣጫ ሄደ ያ አቅጣጫ የመኪና መንገድ የሴለው መሆኑንም አውቃለሁ አየር ማረፊያው አካባቢ አንድ መጋዘን ቆርቆሮ ቤት ስለነበረ እሱን ተከልዬ ወደ አፈሩ ቤት ተጠጋሁ ታንኩ እኛ አይመጣም ባልንበት መጣ በዚያ ጊዜ ታንኩ ጨፍልቆን መሄድ ይችል ነበር ወይም ተኳሹ ገና ሲያየን ከቅርብ ርቀት ሊመታንም ይችል ነበር ግን አላደረገም አዙሮ ሊወጣ ሲል የሯ ሻለቃ ባልደረባ ባሻ አለማየሁ ቦምብ ወርውርበት ሲለኝ እኔም ከኋላ ተከትዬ ቦንቡን ወደ ቱሬቱ በጥንቃቄ ወረወርኩ ዕድላችን ተሳካና ቦምቡ ታንኩ ውስጥ ገባ ከዚያ በኋላ ቦምቡ ሲፈነዳ ለካስ ልጁ ቆስሎ ኖሯል ወደ ዐኛ ነዳጅ ጣቢያ በቀጥታ ሄደ እዛ ሳይደርስ በፊት ባዶ የነዳጅና የዘይት በርሜሎች ያሉበት ቦታ ላይ ሄዶ ቆመ መሀል በመጣሁበት በዋነኛው ጅጅጋ መንገድ ተመልሼ ስፄድ ሼል ሳንደርስ ወደ አቶ አሰግደው ሆቴል ስንቃረብ ከባንክ ቤቱ ጋ አንድ ቲ የጠላት ታንክ ቆሟል ገንዘብ ለመዝረፍ የቆመ ይመስላል ገና እኛን ሲያየን የተኮሰብን ጥይት ከድልድዩ በላይ ያለውን የቱሪማንቱሪ ዛፍ ቅጠል እንዳለ አረገፈብን ከድልድዩ ሥር ገብቼ ስመለከት ለካ ባንክ ቤቱ ጋ የቀመው ታንክ ነው ከኋላዬ ሬዲዮ የያዘ ወታደር ስለነበር ጠራሁትና ሬዲዮውን ተቀበልኩት ቦዩ ውስጥ ቁጭ ብዬ መቶ አለቃ በኋላ ኮሎኔል ንጉሜ አዱኛን ጠራሁት የት እንዳለ ስጠይቀው ሲኒማ ቤቱ አካባቢ መሆኑን ነገረኝ «ወደታች ትንሽ ውረድና በገበያው በኩል አድርገህ በጥንቃቄ እንድትመጣ በአካባቢው ሌላ ታንክ እንዳለ አላውቅም አንድ ታንክ ግን ጀርባውን ወደ አንተ አድርጎ ባንክ ቤቱ ጋር ዖር ቆሟል» አልኩት ንጉጫ አዱኛ በጥንቃቄ ወረደ ምንም ነገር አላጋጠመውም ወዲያው ያንን ታንክ አጋየው እኔ በስተሰሜኑ አቅጣጫ ወዳለው ወደ መንዜ ሠፈር አግረኛ ይገር ፄድኩ በዚያን ቀን ቶጋ ወንዝ በጣም ሞልቶ ስለነበር አካባቢው ጭቃ በጭቃ ሆኗል ታንኮች ሲሸሹ ጭቃ ውስጥ ገብተው ቆመዋል ግን አልተመቱም አኛም በዚያ ለማለፍ ምቹ ሆኖ ስላላገኘነው እንደገና ወደ ዋናው የጀጆጅጅጋ መንገድ ተመለስን የሶማሌ እግረኛ ወታደር ለመሸሽ ከወዲያ ወዲህ ይተራመሳል እኛም ማሳደዳችንን ቀጠልን መአ ተስፋዬ የተባለ ባለ አፈሙዝ የአየር መቃወሚያ የያዘ አብሮን ነበር ከአንድ የበቆሎ ማሳ ውስጥ ገባን አሳሹ ቡድን አልፎ እኔም አነሱን ከኋላ በመከተል ላይ አያለሁ አሳሽ ቡድን ያላየው አንድ የሶማሌ ወታደር ክላሽንኮሹኩን ይዞ ከበቆሎው ማሳ ውስጥ ተኝቷል አኛን ሲያይና ቀና ሲል የአየር መቃወሚያ መኮንኑ ከመኪና ላይ ሆኖ ተመለከተው ጌታዬ» ብሎ ጠራኝ እጁን አፉ ላይ አደረገና በምልክት እንዳልንቀሳቀስ አስጠነቀቀኝ ከዚያ በቅጽበት ከኋላ መጣና መታው ያ የጠላት ወታደር ፍርዛት ይዞት ነው እንጂ በያዘው ክላሽ አንድ ካርታ ጥይት ቢለቅብን ኖሮ ሊጨርሰን በቻለ ነበር የጠላት ጦር ምን ያህል ልብ የሌለው መሆኑን በዚህ መገመት ይቻላል ከዚያ በኋላ በደገሀቡር መንገድ ያመለጠን አንድ ታንክ ብቻ ነበር በለፈኤሳ መንገድ በኩል ደግሞ አንድ ታንክ ሲፈረጥጥ ሙሉጌታ ታምራት ተከትሎት አሳደደው ሙሉጌታን በሬዲዮ ጠራሁትና ከፊት ለፊት ምን እንዳለ ስለማይታወቅ ማሳደዱን ትቶ ወደ ኋላ እንዲመለስ ነገርኩት አየር ኃይላችንም በወቀቱ ከዐ በላይ የሚሆኑ መድፎችንና ታንኮችን አጋይቷቸው ነበር ምንም እንኳን የእኛ የሰው ኃይልና መሣሪያ በጣም አነስተኛ ቢሆንም የጠላት ጦር ሊያደርስ ማፍ እ ሻእጋችጋጋዒጋእኋእ ጨጨ መመ ሽ የሞከረውን ጥቃት ተቋቁመን ድል አደረግን ይህ ሁሉ ሲሆን ውጊያው ከተከፈተበት ጊዜ ጀምሮ ምግብ አልበላንም ጓደኞቻችን ነ ላይ ሲወድቁ ስናይና ስንሰማ በእልህና በወኔ እንዋጋ በር በቀጣዩ ቀን ነሐሴ ቀን ዓም ውጊያ አልነበረም በሽሸት ላይ የነበረውም የጅጅጋ ነዋሪ እየተመለሰ ወደ ቤቱ መግባት ጀመረ ጠላት ግን እንደገና ከየቦታው ኃይሉን በማሰባሰብ ወደፊት ገፍቶ መጣ አኛ በወቅቱ ተተኪ ኃይል አልነበረንም የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ሊቀመንበር ሌተና ኩሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ውጊያውን ለመምራትና ሁኔታውን ለማየት እዚያ አካባቢ የመጡት ያን ዕለት ነው የጥገና ቦታና ድርጅታችንን ያደረግነው ካራማራ ላይ ስለነበረ ሊቀመንበሩ ገስጥ የሚባል አንድ መድፈኛ ሻለቃና ከኦጋዴን ውጊያ ተርፎ የተመለሰ የኛ እግረኛ ብርጌድ ይዘው ሲደርሱ ፋፈምና ቆሬ ላይ ውጊያ ገጠማቸው አንድ ብርጌድ የሚሆን ሽፍታ ገብቶ ስለነበረ ያንን ደምስሰው መጠ ያን ቀን የተመቱትን ታንኮች ከየቦታው እያሰባሰብን የአንደኛውን እቃ ወደ ሌላው በመቀየር ጥገና አካሄድን ይህንን ካላደረግን ደግሞ ብዙም ውጊያውን መግፋት አንችልም ምክንያቱም የነበሩን ታንኮች በአብዛኛው ጉዳት ደርሶባቸዋል ከታንክ ጠጋኞቻችን መካከል የጋምቤላው ተወላጅ ቶማስ ቱቲ በጣም ጎበዝ ስለነበረ አሜሪካ ተልኮ የታንክ ጥገና ተምሯል በውጊያ ላይም ቢሆን አንድ ታንክ ሲመታ ገስግሶ ፄዶ የተጐዳውን አካል ከሌላ ከተመታ ታንክ ላይ ፈትቶና ቀይሮ ለውጊያ ዝግጁ ያደርጋል በተመሳሳይ ሁኔታ ባሻ ነጋሽና በአጠቃላይ ቦዚያን ወቅት የነበሩት ታንክ ጠጋኞች ሁሉ እጅግ የሚደነቁ ናቸው ኘሬዚዳንቱ እዚያ ሥፍራ የደረሱት በምሽት ነው ቀደም ሲል አስራኤሎቹ ጅጅጋ ላይ ለታንክ ሥልጠና ሲያሰባስቡን ጎበዝ ተ ተከፈ መጨርር። » አልኩ ለኮሌኔል ኃይሌና ለሻለቃ ጠና ኮሎኔል ኃይሌ አንደነገሩዋቸው ገልጸውልኝ በዚያኑ ፅለት ወደ ሰዓት ገደማ ተመለሱ በማግሥቱ ነሐሴ ቀን ዓም በሶማሌ ኃይል ላይ የማጥቃት ዘመቻ እንድናደርግ ተወሰነ የማጥቃት ውጊያ መደረግ ያለበት ደግሞ የኃይል ሚዛን ከጠላት ኃይል ሚዛን አይሎ ሲገኝ ብቻ ነው የእኛ ኃይል ደግሞ ከሶማሌ ኃይል በጣም ያነሰ በመሆኑ በዚህ አነስተኛ ኃይል መከላከል እንጂ ማጥቃት አይቻልም በዚያንም ፅለት የኛ ክፍለ ጦር ቀዳሚ መምሪያ አዛዥ በወቅቱ ኮሎኔል በኋላ ብጄኔራል እሸቱ መኮንን ነበሩ የማጥቃት ትዕዛዝ ሲሰጥ መቃወም አይቻልም ቢያንስ ሁኔታውን ገልጾ ለማሳመን አለቆቻችን ሞከሩ ለማንኛውም ጠላት ጦሩን አሰባስቦ እዚሁ አለንበት ድረስ መምጣቱ የማይቀር ነው እዚችው ጅጅጋ ከተማ ከአሉት ቤቶች ጥግ ሥር አነዚህን አነስተኛ ታንኮች ደብቀን ሲመጡጠብን ወጣ ብለን ብንመክታቸው ይሻላል የእነሱ መድፍ በቀጥታም ዞነ በሥውር ሲመታን ይችላል የእኛን ታንክ ያቃጠለው የእነሱ ታንክ ሳይሆን መድፋቸው ነው» የሚል የማሳመኛ ክብ ቢቀርብም የሚሰማ አልተገኘም ስለዚህ በሁለት አቅጣጫ ለመግፋት ተገደድን የሰሜኑ አቅጣጫ ወደ ለፌኤሳ ሲሆን የምሥራቁ አቅጣጫ ደግሞ ወደ ደገሃቡር መንገድ ነበር በሰሜኑ በኩል የኃይል አሰላለፉ ኛ ብርጌድ ከኛ ሻለቃ አንድ ሻምበል ኢም«ጩጳ ታንክ ሲሆን በምሥራቅ አቅጣጫ ደግሞ ናዷ መድጐፍ በሌተና ኮሎኔል በኋላ ብርጋዴር ጀኳራል ጌታቸው ዛይናን የሚመራ መድፉ ብረት ለበስ ላይ የተጠመደ ስለነበር እንደ ታንክ ከአግረኛው ፊት በመሆን ከአንድ ቫለቃ የማይበልጥ የሚሊቪያ ኃይል ኤም ታንክና ከኛ ሻለቃ የተውጣጣ ሻም ር ነበር በህለቁም አቅጣጫ የተቀነባበረ ውጊያ ያደረገው የወገን ጦር ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ጠላትን ከጅጅጋ ከተማ አካባጃ ገፈተረ በሰሜን አቅጣጫ በተደረገው ውጊያ ኤም ታንኮች በወገን በኩል መቃጠሉ ትልቅ ጉዳት ሆነ በምሥራቅ የገፋው የወገን ጦር ገርባሳ ካምፕን አልፎ መልሶ ሬክ አደረገ በዚህ ዕለት ዉጊያ ላይ የተሳተፉት ኤፍ ጀቶች አንድ ካምቤራ ቦምብ ጣይ አውሮፕላን ለጊዜው ወገን ሊደርስበችሽ ያልቻለውን መድፎችና አየር መቃወሚያ መሣሪያዎትን ናከር ሲንቀሳቀስ የነበረውን የጠላት ኃይልና መሣሪያ ደግመወ ደጋግመው በሚያኩራ ሁኔታ አጋዩት ከነሐሴ እስከ ጳጉሜን ቀን ዓም ድረስ ወገን ባደረገው የመከላከል ውጊያ ጥሩ ውጤት ያገኘ ሲሆን ጳጉሜን ቀን እንዲያውም ግንባሩ ፀጥ ብሎ ዋለ ጠላት በጅጅጋ ግንባር ያሰለፈው አንድ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር አንድ ታንከኛቨ አንድ መድፈኛ ብርጌድ አንድ አየር መቃወሚያ ብርጌድና ከሦስት ስኳድሮን የማያንሱ አውሮፕላኖች ሲሆን ይህ ግዙፍ ኃይል ኩርማን በማይሞላ የኢትዮጵያ ሠራዊት ከላይ በጠቀስኳቸው የውጊያ ቀናት በመደምሰሳቸው ጠላት የእኛን የውጊያ ትጥቅ መጎዳቱን በማወቅ አጋጣሚውን ተጠቅሞ ቀድሞ ኦጋዴንን ከያዘበት ኃይል ከቀብሪደሃርና ከደገሃቡር እንዲሁም ከሃርጌሳ ተጨማሪ ጦር አንቀሳቀሰ ይህ ሁሉ ሲሆን ኢትዮጵያ በደቡብ በሰሜን እንዲሁም በምዕራብና በሌሎች ቦታዎች ከትንሽ እስከ ትልቅ ውጊያ ላይ በመሆኗ በዚያን ጊዜ ሊላክልን የሚችል ምንም ኃይል አልነበረም በዚያን ወቅት በትንሹ ታንኮችና ቢኤም እና አንድ ሜካናይዝድ ሻለቃ ቢኖረን ውጊያው ፍፁም ሌላ መልክ ይዞ የድል ባለቤት በሆን ነበር ይህ ባለመሆኑ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ በአዲስ መልክ ጳጉሜ ቀን ዓም በሮኬትና መድፎች እጅግ በሚዘገንን ሁኔታ የወገንን ይዞታ ቀጠቀጠ በዚሁ ዕለት ሁለት የጠላት ሚግ አውሮፕላኖች በወገን ላይ ጉዳት ለማድረስ በተለይ ገርባሳ አካባቢ ባሉት ታንኮች ላይ ሮኬት ቢተኩሱም ምንም ጉዳት አላደረሱም በአንፃሩ ከወገን አየር መቃወሚሜያ ታንኮችና የማዘዣ ብረት ለበሶች ካሊበር ላይ የተተኮሱት ጥይቶች አንዱን ሚግ አንበሳ ተራራ ላይ ሲያጋየው ለመጀመሪያ ጊዜ በዣንጥላ በመውረድ ሳይ ያለውን የሶማሌ ፓይለት በአየር ላይ መግደል ሲቻል የዓለም አቀፍን ህግ ብቻ በማክበር ፓይለቱ መሬት ከነካ በኋላ እርሱን ለመማረክ በተደረገው ግብ ግብ የወረደበት ቦታ ለሶማሌዎቹ ጦር ቅርብ ስለነበረ ሊያመልጥ ቻለ በዚህ ፍልሚያ ከኛ ወገን ጓዶቻችንን አጣን ይህ በእንዲህ አንዳለ ለጊዜው በማንና እንዴት እንደሚሠራጭ ሳይታወቅ «ጠላትህ ያለው መፃዛል ሀገር ነው ። እኔና የሬዲዮ ኦኘሬተር ብቻ ነን የተረፍነው እንዳለ ሠራዊቱ አልቋል» እያለ አንድ ድምጽ በፍርሀት ተውጦ ይለፈልፋል የሶማሌ አዛዥ መኮንን ስለነበር ለኛ የልብ ልብ ሰጠን አየር ኃይላችንም የምናስተላልፍለትን መልዕክት በሚገባ እየተቀበለ የሶማሌ ጦር ቁስለኛውን ይዞ ጥዋት ላይ ሲፈረጥጥ እየተከታተለ ደበደበው ጠላት መፈናፈኛ አላገኘም ውጥረቱ በጠላት ላይ እያየለ ሄደበት በመቀጠል ከደገሀቡር ወደ ጅጅጋ አንድ ሻለቃ ጦር ልኬልፃለሁ» የሚል አንድ የሶማሌ መኮንን መልዕክት በወገን ተጠለፈ ጥሩ አጋጣሚ ሆነ ከደገሀቡር ጅጅጋ ለሚጓዝ ሠራዊት ቀብሪበያህ እስከሚደርስ በጉዞው የሚያጋጥመውን ቁጥቋጦና ጫካ ከግምት ውስጥ አስገባን ከቀብሪበያህ እስከ ጅድጋ ያለው መንገድ ሜዳማ ስለሆነ የሚደርስበትንም ጊዜ ገመትን ከሁለት ሰዓት ጉዞ በላይ አይፈጅም የወገን መኮንኖች ይህንን የጠላት መልዕክት እንዳገኘን ከመቅጽበት ተነጋገርንና ተስማምተን ውሳኔ ላይ ደረስን የውሳኔአችን መልዕክት ለአየር ኃይላችን ተላለፈ የጠላት ጦር ቀብሪበያህን አልፎ ሜዳማ ቦታ ላይ ሲደርስ አየር ኃይላችን ተከታትሎ አመድ አደረገው የወገን ሠራዊት በወቅቱ ከነበረው ጠንካራ ጐን አንደኛው የጠላትን የሬዲዮ መገናኛ እየጠለፈ ጠላት ሊያደርስ የሚችለውን ጥቃት በማክሸፍና በመቀነስ በአንጻሩም ለወገን ጦር ድልን ማስመዝገብ ነው እዚህ ሳላይ ያኑ በጠለፋው ሥራ ላይ ከፍተኛውን ሚና የተጫወቱት ሻምበል አስራት አየለ የኛ ክፍለ ጦር ቀዳሚ መምሪያ የመረጃ መኮንንና የሬዲዮ ኦፕሬተሮችና ሚስጥር ፈቺ ክፍሉች ናቸው ተሩ ው መሽ በዚህ ውጥረት ላይ እያለን ነበር የሶቪዬት ሕብረት አዳዲስ ታንኮች የወገን ጦር የሚታጠቅ መሆኑን የሰማነው እነዚህ ታንኮች ከአሰብ ተነስተው አዋሽ አርባ ላይ ደርሰዋል እነዚህን አዳዲስ ታንኮች ታጥቀን ወደ ጦር ግንባር እንድንገባ የበላይ አካል መመሪያ ሰጠ በዚያኑ ምሽት አለቃዬ ሻለቃ ጠና ጋሻው አንድ የሶማሌ መድፍ ጥይት በተቀመጡበት ቦታ አቆሰላቸው ሻለቃ ጠና ጋሻው ቀልደኛ ረጋ ያሉ ድፍረትና ጀግንነት የተላበሱ መኮንን ሲሆኑ በማግስቱ ሐረር ሆስፒታል እንደገቡ ህይወታቸው ሲያልፍ ለፈፀሙት ጀብዱ በ ዓም የጀግና ሜዳሊያ ኛ ደረጃ ተሸላሜ ሆነዋል እኛ ከኛ ታንክ ሻለቃ የተረፍነው ጥቂት መኮንኖችና ባለ ሌላ ማዕረጎች ወደ ናዝሬት እንድንሄድ ተደረገ አኔም ከነዚህ ውስጥ አንደኛው መኮንን ነበርኩ ቤተሰቤን ከሐረር ይዝ በመጀመሪያ ናዝሬት ገባሁ ማረፊያ አልነበረኝም ናዝሬት በር እንጂ መስኮት ያልተገጠመላቸው የቁጠባ ቤቶች ለመኖሪያነት ተሰጡን አልጋ ፍራሽ የሚባል ነገር የለም ይህንን ለማሟላት አቅሜም አይፈቅድልኝም ከጅጅጋ ስወጣ ሙሉ ንብረቴን ትቼ የለበስኪኳትን ልብሴን ብቻ ነው ይገር የሄድኩት ለግል ሕይወቴ የማስብበት ጊዜ አልነበረኝም መስኮቶቹን በካርቶን እንዲሸፈኑ አደረግን ከመንግሥት በኩል ለቤተሰብ የሚሆን አንድ ብርድ ልብስ ብቻ ተሰጠን ቤተሰቤን በዚህ ዓይነት መልኩ አሳርፌ ወታደራዊ ግዳጄን ቀጠልኩ የኔ ጉጉት ግን አዲሶቹን ታንኮች ይዘን ወደ ጦር ግንባር የምንዘምትበትን ቀን እየሠሩ በተስፋ መጠበቅ ነበር ታንኮቹን ተረክቦ ድርጅቱን የማሙዋላት ሥራ ጠበቅን የኔ የሥራ ድርሻ በየቀኑ አዲስ አበባ እየተመላለስኩ ድርጅት ማሙዋላት ሆነ ይህንን ሥራ እንድከታተል ያዘዙኝ ኮሎኔል ኃይሌ ተስፋሚካኤል ናቸው ዴውኹጮ ኣሥ ው ችው ች ኮሉኔል ኃይሌ ተስፋሚካኤል በጣም የማደንቃቸው ሀቀኛ መኮንን ነበሩ መኮንኑ የሶማሌ ወንበዴ ገና በምሥራቁ አካባቢ መንቀሳቀስ ሲጀምር ችግሩንና መወሰድ ያለበትን አርምጃ በየደረጃው ሪፖርት በማድረግ ነገሩ ከመባባሱ በፊት ቢያሳውቁም የሚሰማቸው አላገኙም ኘሬዚዳንት መንግሥቱ ወደ ምስራቁ ጦር ግንባር በመጡበት ወቅትም ቢሆን አባካችሁ ተጨማሪ ኃይል ተልኮልኝ ይህንን ጦርነት በጊዜው ልቅጨው እያሉ ሰሚ አላገኙም ለምድር ጦር ጠቅላይ መምሪያና ለመከላከያ ሚኒስቴርም በተደጋጋሚ አመልክተው የሰማቸው አልነበረም ይህ ብሶታቸው ድንገት ገንፍሉ ሱልጣን ኢብራሂም አሰብን አንደሸጠ ሁሉ ኃይሌ ተስፋሚካአል ደግሞ ካራማራን ሸጠ መባልን ስለማልፈልግ ኃላፊነትን ለሚያስረክቡት ሰው ያስረክበቡ» በማለት ሊቀመንበሩን አስከ መጠየቅ ደረሱ ሊተመንበሩም በወቀቱ ጥያቄውን ተቀበሉና የዚያን ጊዜ ኮሎሄል በኋላ ጀነራል ይልማ ግዛው እንዲረከቡት አደረጉ ኮሎኔል ኃይሌ ተስፋሚካኤልም ወደ አዲስ አበባ እንዲሄዱ ተወሰነ ኃይሌ በአጹ ኃይለሥላሴ ጊዜ የቀኃሥየጦር ሜዳ የጀብዱ ሜዳሊያ ባለ ሶስት ዘንባባ ተሸላሚ ናቸው ነገርን ያሳያል ቀደም ሲል ለሊቀመንበሩ የጠየቁት ጥያቄ ካልተሟላ እንዲረከባቸው ለሊቀመንበሩ ጥያቄ ሲያቀርቡ አንዲሄዱ የተደረገው ለምን አንደዚህ ተናገርክ ሊወስዱባቸው ይሆናል የሚል ግምት ነበረን በዚህ ጉዳይ ላይ በደርግ ጽቤት ስብሰባ የነበረውን ችግር አስረድተው ኃላፊነታቸውን መንግሥት ወደ አዲስ አበባ ብለው እርምጃ በአንፃሩ ደግሞ ተጠርቶ ዴዴ መች መቼም ጊዜ ብዙ ። መድፈኞች አብረውኝ ነበሩ ጎበዝ ኢትዮጵያዊ ጀግኖች ናቸው የኢደጋን መንደር እንዳለፍን ፎርቶ ወለል ብሎ ታየን መንገዱ ሁሉ በፈንጂ ታጥሯል ቢባልም በፍልሚያ ላይ ከነበሩት አንደኛ ውን ሜካናይዝድ ሻምበል ከሁለት ታንኮች ጋር አስፋልቱን በቀጥታ ይዘው አውሮኘላን ማረፊያውን እንዲይዙ ሌላው ሻምበል ደግሞ ይህንኑ መንገድ ተከትሎ ከአጂኘ ቀጥሎ ያለውን ተረተር እንዲይዝ ትፅዛዝ ሰጠሁ ይህንን በምናካሂድበት ወቅት በየጉራንጉሩ ስር የነበረው የሻዕቢያ ጦር እየሸሸ መውጣት ጀመረ የጠላት ጦር በምሽጉ ውስጥ ለብዙ ቀናት ስለቆየ ሰውነቱ ተሳስሯል በአየር እጦት ታፍኖና በፃሩርና በጭስ ተጎድቷል ከምሽግ ውስጥ እየወጣ በመሮጥ ላይ እንዳለ ጉልበት ስላነሰው ይውድቃል ከእኛም ከኛ ብርጌድ ውስጥ ወደ ዐ የሚደርሱ የሠራዊቱ አባላት በፀፃይ ዛናሩሩና በቃጠሎው ህይወታቸው አልፏል በተለይም የእኛ አግረኛ በውጊያው ላይ ባገኘነው ድል በሞራል ሲሮጥ እየወደቀ ህይወቱ ያልፍ ነበር ፎርቶን ስንይዝ የሻዕቢያ ሃይሎች ሞርታርና አንዳንድ አቃዎቻቸውን ለመውሰድ አንድ ኤንትፊ መኪና ሲያመጡ የእኛ ልጆች ደግሞ ቀድመው ፎርቶን ተቆጣጥረውት ስለነበር የነሱን መኪና በታንክ መቱት ከዚህ ሽንፈት በኋላ የሻዕቢያ አዛዥች በቢጫ ዳትሰን ውልቅ ብለው ሽሽት ጀመሩ ከአስመራ ወደ ምፅዋ የሚመጣ ኤፍ ኢ መንገድ ላይ አግኝቶ ደመሰሳቸው በዚያ ዘመቻ ከምፅዋ አምልጦ የወጣ የጠላት ከባድ መሣሪያ የለም ኛ ብርጌድ የግራ ክንፉን ያዘ ኛ ብርጌድ ደግሞ ቀኙን ተቆጣጠረ ኛ ብርጌድ ደግሞ አካባቢውን በሚገባ ሳይዘጋው ኖሮ እስከ ሲሚንቶ ፋብሪካ ተቆርጠው ከቀሩት የሻዕቢያ ወታደሮች ጥቂቶቹ በባህሩ ጥግ ጥግ ሌሊቱን ማምለጥ ቻሉ ከጠዋቱ ሰዓት ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ፎርቶ ላይ እንተክላለን ሚል ዛሳብ ነበረን ያቀድነው አልቀረም በአሰብንበት ሰዓት ኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ፎርቶ ላይ አውለበለብን ይህ ብብ ፎጭጭጭዌጭጠሎጭጭጭጭጠ ሯጮ ሽሽ የጦር መርከቦች ለሠራዊቱ ታላቅ ኩራትና ደስታን አስገኘለት የውጊያ ሞራሉንም ዘመቻ አሉላ ሐምሌ ዓም ለተጨማሪ ድሎች አነሳሳው ሻዕቢያ የምዕዋን ምሽግ የሠራው ከአስመራ እስከ ምፅዋ ተዘርግቶ የነበረውን የባቡር ዛዲድ ብረት ነቃቅሎ ነው ምሽጉ በጣም ጠንካራና ኃይለኛም ነው እንደዚያ የተሠራ ምሽግ በህይወቴ ሙሉ አላየሁም ከዚያ ውስጥ ነው የሻዕቢያን ጦር ቆራጥነት በተመላው ወኔ ሰብረን ያወጣነው ሙሉ ቆራጥነት የታየበት ውጊያ ነበር የ ሻለቃ አዛዥ የሻለቃ ሰይፉ ጋሻው ጆሮ በመድፍ ጩኸት የተነሳ ጉዳት ደረሰባቸው እሳቸው ግዳጃቸውን ለመቆጣጠር ከማይችሉበት ደረጃ ደረሱ እኔ የኛ ሻለቃ አዛዥነትን ደርቤ እንድሰራ ተደረገ የእኛ ጦር ፎርቶ ላይ ስለነበር ዶጋሊ በግልጽ አይታይም ዶጋሊ ያፈገፈገው የጠላት ፃይል የመሸገባት ሥፍራ ናት አንድ ሻምበል ሜካናይዝድ ጦር አውጥቼ ወደ ዶጋሊ ቅኝት ጀመርኩ ልክ ኪሜ ገደማ ላይ ስደርስ ዶጋሊን ፍንትው ብላ አየኋት ቅኝቱን እዚያው ላይ አቆምን የቆምኩባት መሬት ጥሩ ገገር መሬት ናት የዘመቻው ግብረኃይል አዛዥ ጀኔራል አበራ አበበ ሲሆኑ ሁኔታውን ለቅርብ አለቃዬ ለኮሎኔል ብርዛፃነ ደምሴ ሪፖርት አደረግሁ «አሁን ዶጋሊን እያየሁ ነው ጥሩ ገገር መሬት ስለሆነ መጥተው ቢመለከቱት» አልኳቸው አሳቸውም ወዲያውኑ መጥተው አዩት «በል አንተ ራስህ እዚህ ቦታ ላይ እንድትቀመጥ አንተ ከምትመራው የተሻለ ጠንካራ ጦር የለንም አሉ ጀኔራል አበራ አበበ በምፅዋ ግንባር ከሲሚንቶ ፋብሪካ እስከ ሲኒማ አይዳ የመሸገው የሻቢያ ኛ ብርጌድ ሲሆን ኛ ብርጌድ ከሲኒማ አይዳ እስከ ሼል ነዳጅ ዲፖ ነበር ተጠባባቂ የነበረው ኛ ብርጌድ ከጥቂት ቀናት በፊት ወደ አስመራ ግንባር ሄዶ ነበር ዘመቻ ዳግማዊ አሉላ ከጦር ግንባሩ ኪሜ ወጥቼ ዐ የዙሪያ ጥበቃ ቦታ ያዝኩ አንድ ሻምበል ጦር ከ ኛ ሻለቃ ተደረበልኝና የመከላከልና የቅኝት ሥራዬን ጀመርኩ በጣም የማደንቀው ነገር ቢኖር መድፍ አስተኳሹም አውሮኘላን አስተኳሹም ከእኔ የተለዩበት አንድም ቀን አልነበረም ማታ ማታ ቃሺ እያወጣሁ በጠላት ላይ ስንተኩስ እናድራለን ሆን ብለን የጠላትን ይዞታና ምሽግ ለማወቅ የምናደርገው ነው በዚህም ስልት የጠላትን ጠንካራና ደካማ ጎኖች በሚገባ ለማወቅ ቻልን ጊዜው ሲደርስ መከላከያ ቦታውን ለሌላ ጦር አስረክቤ ለማጥቃት ዝግጅት እንዳደርግ በስሚንቶ ፋብሪካ አጠገብ ሰፈርኩ የማጥቃቱ እቅድና አቅጣጫ ስለተነገረኝ ህዳር ቀን ዓም የማጥቃቱ ትዕዛዝ ተሰጠ በአኔ የሚመራው ጦር አንዲያጠቃ ትዕዛዝ የተሰጠው መሃሉን ነወ ይሄንን ትዕዛዝ አልተስማማሁበትም ቀደም ሲል ባጠናሁት የቅኝት ውጤት መሠረት የጠላት ደካማ ጎን ጎልቶ የሚታየው በስተቀኝ በኩል ነው በኋላ ፅኛ ብርጌድ ከዋናው መንገድ በስተግራ በኩል እኔ የምመራው ሻለቃ በስተቀኝ በኩል እንድናጠቃ ተወስነ ይህንን ግዳጅ ተግባራዊ ለማድረግ ሳምንት ያህል ጊዜ ነበረን ሻዕቢያ በይዞታው ስር ያደረገውን ቦታ የሚመስል ከአካባቢያችን መረጥኩና የውጊያ ስልታችን ምን መምሰል እንደሚኖርበት ልምምድ ማድረግ ጀመርን ሳምንት ሙሉ ያለ ማቋረጥ ተለማመድን ህዳር ቀን ዓም ጊዜው ሲደርስ ልክ ከንጋቱ ስዓት ተኩል ላይ ውጊያ ተጀመረ ቀኝ ቀኙን አስፍተን በመፄድ የመጀመሪያው ሻምበል የጨበጣ መስመር እንዲገባ ትዕዛዝ ሰጠሁ ሻዕቢያ ምሽጉ ላይ ሆኖ ሲተኩስ የእኛ ብረት ለበሶች ተመቱ አዚያው ላይ እንደተገታን ከንጉሴ አዱኛ የተደረቡልኝን ዐ ታንኮች የተኩስ መደብ በማድረግ አስፈላጊውን ሠጄ ኤሬ ኣፎ ሽፋን መስጠት ጀመርን በዚህ ሁኔታ የተገታውን መካናይዝድ ሻምበል «ከብረት ለበሱ ላይ ወርዳችሁ በልባችሁ ተስባችሁ በምሽጉ ላይ ቦንብ ወርውሩኩ የሚል ትዕዛዝ ሰጠሁ እኛ ከላይ የተኩስ ሽፋን ስንሰጥ እግረኛው በደረቱ ተስቦ ቦንቡን ወደ ምሽጉ ወረወረፊ ምሽጉ ያኔ ተሰበረና ገባንበት በዚህን ወቅት ነበር ጀግናው የመቶ አለቃ አያሌው በውጊያው ላይ ከቀኝ በኩል አስፍቶ ወደ ጀርባ አቅጣጫ ሲገባ በጨበጣ ተኩስ ላይ ከሻዕቢያ ጦር የተተኮሰ ጥይት ደረቱ ላይ መትቶት መስዋዕት የሆነው አስደሳቹ ጉዳይ በዚያ የትግል ወቅት የእኛ መቶ መሪዎች እነ መቶ አለቃ መሥፍን መቶ አለቃ አለም መቶ አለቃ መንግሥቱ መቶ አለቃ መኳንንትና በአጠቃላይ ሌሎችም ጎበዞች ነበሩ እንደምንም ብለን የሻዕቢያን ምሽግ ናድነውና ሁለተኛውን ግንባር ሰብረነው የዶጋሊን ከፍተኛ ገገዢ ወታደራዊ መሬት በቁጥጥር ስር አደረግን ለኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ግብ ተደርጎ የተሰጠን ከዶጋሊ ድልድይ ግራና ቀኝ ያሉት ጉብታዎች ሲሆኑ የኔ ሻለቃ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በሁለቱም ጉብታዎች ላይ በድል አውለበለበ የውሃ ማጠራቀሚያ ያለበትንም ቦታ ተቆጣጠርነው የመጀመሪያው የምዕዋ ውጊያ የዘመቻ ስም አሉላ ሲሆን ይፄኛው ደግሞ ዳግማዊ አሉላ ተባሰ አብዛኛውን ጊዜ በሠራዊቱ ደንብ አንድ ግብ ከተያዘ በኋላ ጦሩ ባለበት ሆኖ መልሶ መቋቋም ያደርጋል በዚህ መሠረት እነም ጦሩ መልሶ መቋቋም እንዲያደርግ ጊዜያዊ ምሽግ እንዲያዘጋጀ ትዕዛዝ ሰጥቼ የጠላትን ሁኔታ ለማጥናት በቀኝ በኩል ካለው ትልቅ ከፍታ ቦታ ላይ ወጥቼ የሚከተለውን ታዘብኩኝ ተደም ሲል ዶጋሊን ጠላት ሲያስለቅቅ በዚያ ቦታ ላይ የገደላቸውን የአኛን ሚሊሺያ ወታደሮች አስከሬን ሰብስቦ ያቃጠለ ር ሲሆን ቀሪውን የአጥንቶችና የጭንቅላቶች ቅሪት አየሁ በሚቀጥለውም ቀን ህዳር ቀን ዓም ወደ ማይጣል ስንነቃነቅ በተመሳሳይ ሁኔታ የተሰው ወታደሮቻችንን አስከሬን መንገድ ላይ አጋድሞ ነጋ ጠባ የመኪና መመላለሻ አድርጎ አጥንታቸው ደቅቆና ዱቄት ሆኖ ተመለከትኩ በእውነቱ ሻዕቢያ ምን ዓይነት ጨካኝ አረመኔና የጣሊያን ፋሺስት ወራሪ ጦር በወገናችን ላይ ካደረሰው ዘግናኝ ድርጊት የከፋ መሆኑን ሕሊና ያለው ሰው ብዙ መረዳትና የራሱን ፍርድ መስጠት ይችላል በመካከላችን የዓላማ ልዩነት ቢኖርም የአንድ ሀገር ዜጐች በሁለት ጐራ ተከፋፍለው በሚካሄደው ዉጊያ ይህ ዓይነት ኢሰብአዊ ድርጊት መፈፀም አልነበረበትም የምሥራቁን ሀገራችንን ክልል ከሶማሌ ወራሪ ወታደሮች ለመከላከል ሲባል በተካሄደው እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንኳን ያን የመሰለ ጭካኔ የተመላበት ሁኔታ አልተፈጸመም እነዚህ ጠላቶቻችን ለሀሰት ኘሮፖጋንዳቸው ያመች ዘንድ የኢትዮጵያ ወታደር ሴትን በሳንጃ ወግቶ ሺሏን ዘርግፎ ይገላል እያሉ የሠራዊቱን ስም በሀሰት ያጎድፋሉ ግን ትውልድና ታሪክ ወደፊት ጊዜውን ጠብቆ ከሚያሳየን ባሻገር የምለው አይኖረኝም ህዳር ቀን ዓም በመቶ አለቃ ሰላሙ የሚመራው ወደ ማይጣል በር እንዲያጠቃ በቅርቡ ከአሰብ ለዚሁ ተደራቢ ሆኖ የመጣው ዐኛ ሻለቃ በቀጥታ በበሩ በኩል ወጣ እንዳለ ጠላት ከፊት ለፊት ካለው ገዢ መሬት በመትረየስና በካሊበር እንቅስቃሴውን ከመግታቱም በላይ ከባድ ጉዳት ማድረሱን እንደተመለከትኩ ወዲያው ከማዘዣ ቦታዬ ወርጄ በስተቀኝ ያለውን ደረቅ ወንዝ ከቃኘሁ በኋላ ብረት ለበሶችን በአንድ ተራ የሚያስኬድ መሆኑን ተረዳሁ ተ መ ከወደ ምዕራቡ በኩል ወጥቼ በሩ ማሳለፍ የሚችል መሆኑን እንዳረጋገጥኩ ሻምበል ንጉጫሜ አዱኛ አንድ ታንክ የመቶ ወደ በሩ በማስጠጋት የተኩስ ሽፋን እንዲሰጠን ሁኔታውን ለአዛዢ በሬዲዮ ገለጽኩላቸውና እኔ እንድገባ ፈቃድ ጠየቅሁ ውይይታችንን ሲከታተሉ የነበሩት የግብረኃይሉ አዛዥ ወዲያው ፈቃድ እንደሰጡ ሁለት ሻምበል ብረት ለበስ እየመራሁ በአንድ ተራ በደረቅ ወንዙ ውስጥ አድርገን ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሄድን ከዚያም ተራ በተራ እንደወጣን የጨበጣ አሰላለፋችንን በአስቸኳይ ስንይዝ የጠላት አቀማመጡ ወይም ምሽግ አያያዙ ወደ እኛ ባለመሆኑ ምንም ገዳት ሳይደርስብን እየተኮስን ጋራው ሥር ተጠጋንና ለጩበጣ ወረድን ከአኛ ግራ አስፍቶ ይጓዝ የነበረው የሯ ብርጌድ ቀደም ሲል በማለዳ ትዕዛዝ ቢደርሰውና ቀኝ ቀኙኑ አስፍቶ ቢሄድ ኖሮ ያንን ግብ ያለ መስዋዕትነት እንይዝ ነበር የአኛ ኃይል ማጥቃቱን እንደሰነዘረ ጠላት ቦታውን ለቆ ሲፈረጥጥ እያሳደድን ማስቀረቱን ተያያዝነው በዚያ ውጊያ ላይ ሻዕቢያ ከፈጸማቸው የግፍ ግፎች በጣም ያስገረመንና ያሳከክነን ቢኖር አንድ አድሜው ወደ ዓመት የሚጠጋ የሻዕቢያ ወታደር አንድ ካሊበር ከበቂ ጥይት ጋር ተሰጥቶት ይዋጋል ግን ሁለት አግሮቹ የተቆረጡ ናቸው ግማሽ ጆንያ ብርቱካንና አንድ ጀሪካን ውዛሃ አጠገቡ አስቀምጠውለታል ይህ የአካል ጉዳተኛ ወደፊትም ሆነ ወደኃላ መንቀሳቀስ ተስኖት ይዋጋል አነሱ ከአካባቢው ሽሸተው ጠፍተዋል በአርሱ ላይ የሞት ፍርድ ፈርደውበታል ማለት ነው እሱ ወዲያውነ ተደመሰሰ የሻዕቢያ ጭካኔና አረመኔነት ይህንን ይመስላል ሻዕቢያ እንኳን በአኛ በጠላቶቹ ላይ ቀርቶ በራሱም ወገን ላይ ይህን ዓይነት ኢሰብአዊ ድርጊት የሚፈጽም አረመኔ ድርጅት ነው ምናልባት የኤርትራ ሕዝብ እነዚህን ድርጊቶች ወደፊት ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሲሰማ ብር ሻዕቢያ ምን ያህል በልጆቹ ላይ ግፍ እንደፈጸመባቸውና እንደተጫወተባቸው ሊረዳ ይችል ይሆናል ከዚህ ውጊያ በኋላ ሻለቃዬ ከተደረቡለት ታንኮች ጋር ወደ ማይጣል ሜዳ እንዲገባ ትዕዛዝ ሰጥቼ መልሶ ማቋቋሙን ማይጣል ሜዳ ላይ አደረግን የኛ ብርጌድ ከአሥመራ ወደ ምፅዋ የሚወስደውን መንገድ ግራውን መሬት ሲይዝ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ መልሶ መቋቋሙን ከአሥመራ ምዕዋ መንገድ መሐሉ ላይ አደረገ ኛ ብርጌድ ደግሞ ከአኛ የቀኙን ሥፍራ ያበዘ በዚህ ሁኔታ አዳር አዚያው አካባቢ አደረግነ ወዲያው ጨለምለም እንዳለ ከእምባቲካላ ከጊንዳ ከደንጎሎ በርከት ያሉ መኪኖች መብራት እያበሩ ወደ ታች ጋይተላይ ሜዳ አድርገው ዐወረዱ ሜዳውን ከወረዱ በኋላ ለአይታችን ተሰወሩ ከብርጌድ አዛገሀ ጋር ሁኔታውን ለማረጋገጥ ተገናኘንና አንዳንድ ነጥቦች ላይ ደረስን ኛ ከፊት ለፊታችን ኪሎ ሜትር የሚባል ገገር መሬት አስለ ጠላት እዚያ ለመመሸግና መልሶ ለማጥቃት የሚፈልግ ከሆነ መብራት አብርቶ መጓዝ አልነበረበትም ስለዚህ ሁኔታው ድንገተኛነትን ያሳጣዋል ጠላት የተመታበት ጦር ዐኛና ኛ ብርጌድ ነው ይህ ዶጋሊ ላይ የተመታው ጦር ደግሞ የሸሸው ወደ ሽኢብ አቅጣጫ ነው ወደ ላይ ወደ ዶጋሊ ወይም ኢምባቲካላ አልሸሰም ኛ የጠላት ዋና ዓላማው ድርጅቱን ለማሸሽ ከሆነ ወጠደ አሥመራም ዝግ ከሆነና እኛ ገናተን ጋይተላይ ሜዳ ላይ ከገባን ዓላማውን ማክሸፍ እንችላለን የሚሉት ሶስት ነቦባች ተረቡና ከጦርነት ሥልት ጫወታ ነህ ሀጠበወ አንጻር ስንተነትነው ጠላት የወገን ጦር ማይጣል ላይ ያድራሉ ብሎ ስለማይገምት በሶስተኛው አማራጭ ተጠቅሞ በአስቸኳይ ድርጅቱን ማሸሹ ነው በሚቀጥለው ህዳር ቀን ዓም ኛ ብርጌድ አሰሳውን ወደፊት በማድረግ ኪሜ ን አንዲቆጣጠር ትዕዛዝ ሲሰጠው ኛ ብርጌድ የዶጋሊን ገገር መሬቶች እንዲቆጣጠር ተደርጎ ኛ ብርጌድ በተጠባባቂነት ፅኛ ብርጌድን እንዲከተለው ተወሰነ በዚሁ መሠረት ኛ ብርጌድ ሙሉ በሙሉ ግቡን አየተቀጣጠረ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ አልፎ የጋይተላይን ሜዳ አንዲይዝ ኛ ሻለቃ አልፎ ሳይመሽበት የታችኛውን የደንጎሉ ተረተር እንዲይዝ ታዘክዘ በትፅዛሄጁ መሠረት ግዳጁ ተፈጸመ ማታ ላይ ብርጌድ አዛገቦ አስጠርተውኝ ስለቀጣዩ ዘመቻ ውይይት አደረግን በውይይታችን ላይ የነበረው ግምታችንም አንድ ሆኖ ተገኘ ጠላት ብልጥ ቢሆን ኖሮ ከረባዳማው መሬት ካለው ተረተር ላይ ቢያንስ ቃሺ አንኳን ማስቀመጥ ቢችል የኛን አንቅስቃሴ ያዘገይብን ነበር ባለፈው ሁኔታ የጠላትን የሩጫ ግሥጋሴ ስናገናዝበው ታችኛው ደንጎሎ የኛ ሻለቃ ጠዋት አንደገባ አኔ ውጊያ አስኪገጥሙን ድረስ በታንክና ብረትለበሶች በአሰሳ መልክ ብሄፄድ ለጠላት ጊዜ አለመስጠት ይሆናል ብዬ ያቀረብኩትን ሀሳብ አለቃዬ ደግፈው ኛ ሻለቃ ወደ ታችኛው ደንጎሎሉ ማታውኑ ቃፒ አንዲያወጣ ተደረገ ቃጊሺዎቹ ደግሞ ሁኔታውን እንዲያረጋግጡ ትዕዛዝ ተሰጣቸው ቃፒዎቹም በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት መንደሮቹ ውስጥ ገብተው ምንም የጠላት እንቅስቃሴ እንደሌለ በሬዲዮ አረጋገጡልን ይህ ከሆነ በኋላ ኛ ሻለቃ በመቶ አለቃ ታደሰ ኮሎኔል የሚመራው ታችኛውን ደንጎሉ እንዲቀጣጠር በሬዲዮ ትዕዛዝ ተላለፈለት እሱም በተላለፈለት መመሪያ መሠረት ግዳጁን ፈጸመ በዚህ ጊዜ በአኔ የሚታከዝ ኛ ሜካናይዝ ሻለቃ ክሌ ከላዩ ላይ የተጠመደውን መሣሪያ ግራና ቀኝ በማሰባጠር በአንድ ተራ ጉዞ ወደፊት ቀጠለ ከታችኛው ደንጎሎ እንደደረስን ሕዝቡ ግራና ቀኝ ሆኖ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለበ ተቀበለን ይህ ዓይነቱን ሁኔታ ስንመለከት በእርጋታ ወደ ላይኛው ደንጎሎ ጉዞአችንን ቀጠልን አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ሕዝቡ ተቀበለን ሁኔታውን ለበላይ ሪፖርት አደረግሁ አካባቢውን ሁለተኛ ሻለቃ እንዲይዘው ተደርጎ ወደ ጊንዳ ገ ተጠልን ጊንዳ ስንደርስ የአገር ሽማግሌዎች ባንዲራ ይዘው «ጠላት በዚህ አካባቢ የለም አሁን በዚህ አካባቢ ያለው ሕዝቡ ብቻ ነው አባካችሁ እንዳትነኩን ብለን ለመለመን ነው የመጣነው» ብለው ጠየቁን «እኛ ሕዝባዊና ነዓ አውጪ ነን» ስንላቸው ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ጨፈፊረ ብርቱካንና መንደሪን ለጦሩ አደሉ በዚህን ወቅት ሕዝቡ ወዶ ሳይሆን ተጨቁኖ ታፍኖና ተገዶ መሆኑን ከነበረው ስሜትና አኗኗር ከጉስቁልናውም ጭምር ለመረዳት የቻልንበት ጥሩ አጋጣሚ ነበር ኢምባቲካላ ላይ የጠላት ሠራዊት እንዳለ ሕዝቡን ብንጠይቅም ምንም ዓይነት የጠላት ጦር እንደሌለ አረጋገጡልን ጉዞአችንን ወደፊት ገፋን የሕዝቡ ስሜት ግን ያው ነው ከኢባቲካላ በኋላ ወዲያውኑ ነፋሲትን መያዝ አንዳለብን ለብርጌድ አዛገር ሪፖርት አደረግሁላቸው በተጨማሪም ኛ ሻለቃ በአስቸኳይ እንዲከተለን ሀሳብ አቅርቤ በተፈቀደልኝ መሠረት ወደፊት ጉዞ ቀጠልን ጉዞው በጣም ፈጣን ነው በወታደራዊ የሕይወት ውጣ ውረድ እንደዚያ ያለ የተፋጠነ ጉዞ አጋጥሞኝ አያውቅም ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ የገ አቅጣጫን የሚያመላክተው ወደ ዳገታማ ሥፍራ ማለትም ከባህር ወለል ወደ ላይ ነው ጠሳት በዚያን ጊቬ ቢያገኘን ኖሮ አንድ ቦታ ላይ እንገታ ነበር ስለዚህ በተቻለ መጠን እስከ አሥመራ ድረስ ያለውን መንገድ ሙሉ በሙሉ በአንድ ቀን መክፈት ነበረብን በዚህ መሠረት ቀጥለን ነፋሲት ስንደርስ አሁንም ሕዝቡ አንደተለመደው ወጥቶ በጭብጨባና በአልልታ አልተቀበለንም ሁኔታው ሁሉ ዱብ ዕዳ ሆነበት ሕዝቡ የእኛን መምጣት በፍርዛትና በድንጋጤ ሲመለከት ወዲያው አንደኛ ሜካናይዝድ ሻምበል ከመንደራ ከፍ ያለ ቦታ ላይ እንዲይዝ አድርጌ አሁንም የአካባቢውን አዛውንት አስጠርቼ አነጋገርኳቸው «በዚህ አካባቢ ጥቂት ወንበዴዎች ነበሩ ሆኖም ከትላንት ጀምር ተሰውረዋል አናንተ ትመጣላችሁ የሚል ግምትም አልነበረንም» የሚል መልስ ሰጡን ወንበዴዎች ካሉ መሣሪያቸውን አስረክበው ከሕዝቡ ጋር መቀላቀል እንደሚችሉና ምንም ዓይነት ርምጃ እንደማይ ወሰድባቸው ገለጽኩላቸው ይህ ከሆነ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ሶስት ወንበዴዎች መሣሪያቸውን አስረክበው ከሕዝቡ ጋር ተቀላቀለሉ ከኛ አግረኛ ሻለቃ ከሻምበል ዘውዴ ገጻዲቅ ጋር እርክብክቡን ከፈጸምኩ በኋላ ወደ አሥመራ የአርብ ርብን ዳገት ተያያዝነው ዳገቱ ከባድና ጠመዝማዛ ነው ዳገቱን ለመውጣት ጊዜ ወሰደብን በጉዞ ላይ አንዳለን መስሸብን ቢሆንም ሀሳባችንን ከፍጻሜ ለማድረስ ወደፊት ገፋን በጥበቃ ላይ የነበረው የወገን ጦር የጥይት ውርጂብኝ አወረደብን የወገን ጦር መሆናችን መረጃ አንዳልደረሰው ተረዳን የአጸፋ መልስ በመስጠት ፋንታ ትዕዛዙ ከዘመቻ መምሪያው እንዲሰጣቸው ለአለቃችን መልዕክቱን አስተላለፍን በተላለፈው ትፅዛዝ መሠረት ወዲያው አኛ መሆናችንን ሲያውቁ ጥይት ወደ ሰማይ ተተኮሰ እኛም ዳገቱን አልፈን እንደወጣን በሁለታችን መካከል የሚያግባባውን ምልክትና ሰላማዊ ግንኙነት ስናረጋግጥ እጅግ የሆነ የደስታ ስሜት ተፈጠረብን ፎኤፎጁ ለጊዜው ከመንገዱ በስተቀኝ አንድ ሰፋ ያለ ቦታ ላይ ገብተን አዳር አደረግን ማታ ለአዛዝች ትፅዛዝ ተላልፎ ስለነበረ ብርጌድ አዛዥች ብቻ ጥዋት ሰዓት ላይ አዳር ካደረግንበት ሥፍራ ላይ ደረሱ ትዝ ይለኛል የክብር ዘበኛ የኪነት ቡድን በአንድ አይፋ ላይ ሆነው ወኔ የሚቀሰቅስ ዜማ አሰሙ ኤፍ ኢ ጀቶች በሰማይ ላይ ትርዒት ሠሩ ከታች የሰሜን እዝ አዛኝ ከመምሪያ መኮንኖች ጋር ሆነው ለዐኛ ግብረኃይል አዛሻየ ለኮሎኔል አበራ አበበ የጉንጉን አበባ አጠለቁ ከአዛገየቦቹ ጋር ሰላምታ ተለዋወጠ ይፄ ሁሉ ሲሆን እኔ ከኋላ ጥግ ይገር እመለከት ነበር የኛ ሜካናይዝድ ሻለቃ ወደ አሥመራ ከተማ ገብቶ እንዲወጣ ትዕዛዝ ተስጠኝና በሰልፍ መንገዶቹን ዞረን ተመለስን በአብዛኛው መንገዶቹ ሁሉ በወንበዴዎች ተዘግተው ስለነበር ሕዝቡ እጀግ የተጎዳ በመሆነ ደስታውን ሳይቀጥብ ገለጸልን ከፊሉ ደግሞ ያዘነና ግራ የገባው መሆኑ ከፊቱ ላይ በግልጽ ይነበባል። ሯ ክፍለ ጦር ምፅዋን ተረከበ ዘመቻ አልጌና የዘመቻ አልጌና ዓላማ ከናቅፋ አካባቢ ተመትቶ የሚያፈገፍገው ጠላት ድርጅቱን ይዞ እንዳይወጣ ለመደምሰስ ታስቦ የታቀደ ነበር መጋቢት ቀን ዓም የእኛ ጦር ወደ አልጌና እንዲሄድ ትዕዛዝ ደረሰው አካሄዳችን በሁለት መስመር ነበር ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ታንኩን ይዞ የባህሩን ጠርዝ ተከትሉ በመርሳ ገጉልቡብ አድርጎ ወደ መርሳተክላይ በመርሳተክላይ አድርጎ አልጌና እንዲገባ ሲሆን ፅኛና ኛ ብርጌዶች በጀልባና ላዲንግ ክራፍት በምድረነክ ተጓጉዘው መርሳተክላይ እንዲገቡ ኛ ብርጌድ ደግሞ ምፅዋ አንዲቀርና እዚያው በመከላከል ላይ ካለው የኛ ክፍለጦር ጋር የክፍል አካል እንዲሆን ተወሰነ እንደተለመደው የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ግንባር ቀደም ሻለቃው የኔ የኛ ነው አንድ ታንከኛ ሻምበል ተደርቦልን ጉዞ እንድናደርግ ታዘዘ የምንጓዘው በበርፃማና አሸዋ ላይ ነው ባሻ ንጉሜጫ የሚባል ክብር ዘበኛ የጦር አባላችን ነበር በኋላ አልጌና ላይ ተሰዋ ወደፊት ታሪኩን ደግሜ አነሳዋለሁ ይህንን አካባቢ በሚገባ አንድ በአንድ ያውቀዋል ሌላም ባሻ ደስታ የሚባል ጎበዝ ኮማንዲስት ነበር በኋላ ላይ አንድ እግሩን አጥቷል ሁለቱም ጠላት ያንን አካባቢ ከመያዙ በፊት በንገሥ ዘመን ብዙ ጊዜ ተመላልሰውበታል እያንዳንዷን ቦታና ሁኔታ በዝርዝር ይነግሩኝ ነበር በጉዞ መስመራችን ላይ ውዛ የት ማግኘት እንደምንችል ጠየቅኋቸው መርሣጉልበብ ላይ የጨው ውዛ ማግኘት ቢቻልም ለታንኩም ለብረት ለበሱም ለሰውም አንደማይበቃ ገለጹልኝ በተቻለ መጠን ባለን ነገር ሁሉ ብረትለበሶች ውዛ አንዲይዙ አደረግን በበረዛ ውስጥ ዘመቻ ለማካሄድ ውዛ ወሳኝ ነው መዝጊያ ባለው ቀለህ ውስጥ ሳይቀር ቀዳን ቦቴም ይዘናል ቢሆንም በተለይ በበረሃ ውስጥ ውዛው እየተነነ ስለሚያልቅና የብረት ለበሶችና የታንኮች የማቀዝቀዣ ክፍሎቻቸው በጣም ስለሚግል የበለጠ ስጋቴን እየጨመረው ሄደ አጠቃላይ ትዕዛዙን በሙሉ እኔ ለሻለቃዬ ከሰጠሁ በኋላ አዛዥፐች ደግሞ በደረጃው ዝርዝር ትዕዛዙን አስተላለፉ ከፊት ለፊት አንድ ታንክ የመቶና አንድ ብረት ለበስ የመቶ በቀዳሚ ቀጥሉም ሁኔታዎችን በቅድሚያ ለመመልከትና ትዕዛዝ ለመስጠት ከፊት መሆኑን ስለማምንበት እኔ ራሴ ከዚሁ ጦር ጋር ሁጌ ጥዋት ሰ ዓት ላይ ጉዞ ጀመርን መንገዱ አሸዋማ ነው ገዞ እንደቀጠልን አንድ ቦታ ላይ ስንደርስ ፈንጂ ገጠመንና አንድ ኡራል መኪና ተመታብን በሰው ላይ የደረሰ አደጋ ግን አልነበረም ከዚያ ጉዞ እንደቀጠልን እንደገና አንድ ብረት ለበስ ተመታብን ብዙም ጉዳት ስላልደረሰ ጎማና አንዳንድ ነገሮችን ቀይረን ጉዞ ቀጠልን እለቱን መርሣጉልቡብ መግባት እንችል ነበር ነገር ግን በአነዚህ ጥቃቅን ምክንያቶች የተነሳ በሚቀጥለው ቀን መርሳጉልቡብ ገባን አንዳንድ ዝግጅቶችን ካደረግን በኋላ ጉዚችንን ወደ ፊት ቀጠልን እኛ በጥዋት ጉዞዋችንን ወደፊት ስንቀጥል ዐኛ ክፍለ ጦርም ከነበረበት ተላቆ ከእኛ ጋር ወደ አልጌና አንዲጓዝ ትዕዛዝ ደረሰው ለአኛ ከባድ የነበረው በአሸዋማ በረዛው ላይ የመጓዙ ጉዳይ አንጂ ጠላት በዚያን አካባቢ ለማጥቃት ብቃቱም ሆነ ድፍረቱ አልነበረውም እዚያ አካባቢ ደፍሮ ቢወጣ ኖሮ ከፍተኛ ህልፈት ያጋጥመው ነበር ጉዞው በነጋታው ቀጥሎ መርሳተክላይ ገባን መርሳተክላይ እንደገባን የግብረኃይል አዛዝ ትንሽ ወደፊት ኪሜ ገደማ ሄደን የጥበቃ ቦታ እንድንይዝ ትዕዛዝ አስተላለፉ ትዕዛዙ ደርሶን ቦታ መያዝ ላይ ሳለን ኮሎኔል ገብረ ክርስቶስ ቡሊ ያን ጊዜ የአሥመራ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ የነበሩ በፄሊኮኘተር ከአልጌና አቅጣጫ መጡና እኛ ባለንበት ቦታ አረፉ ምሽቱ አየተጠጋ ነው ወደ ሰዓት ገደማ ይሆናል ኮሎኔል ገብረክርስቶስ ቡሊን በአንዳንድ ሁኔታዎች አደንቃቸዋለሁ ከቆፍጣና መኮንንነታቸው በተጨማሪ አጭርና ረ ር ዑ ፕ ሙኑት ደጋሸር ቄጩ በ ግልፅ ትዕዛዝ ይሰጣሉ በግዳጅ ቦታዎች አንዳንድ ነገሮችን አካባቢውንም መቆጣጠራችንን ወዲያው ለበላይ ሪፖርት አደረግን በአንፃር ተገኝተው ይመሰለከታሉ ለተሰማሩበት ሙያ ራሳቸውን የበላይም ቦታውን ይዘን አዳር እንድናደርግ መመሪያ ሰጠኝ ያስገዙ መኮንን ናቸው ቢሆንም ደግሞ አንዳንድ ድክመቶች መሸት እንዳለ የሻዕቢያ መኪና ከአልጌና የታቤ ሸለቆ ውስጥ እንደነበሩባቸው አብረዋቸው የሠሩ መኮንኖች ቢናገሩም በዚያን መብራት እያበራ ሲወጣ አየነው ዓላማው መንገዱን ይዘጉብናል ጊዜ ካሉትና ወይም ከዚያም በፊት ከነበሩት መኮንኖች ጋር በግል ብሎ ሠራዊቱን ማስመለጡ ነበር እኛ ግን ወደፊት እንዳንገፋ ሳነፃዕራቸው የተሻሉና ብቁ መኮንን ነበሩ ማለት ይቻላል መቼም ጨለማ ነው መድፍ ቢኖረን ኖሮ ባለበት ማስቀረት እንችል ማንም ቢሆን ሁሉንም ነገር አሟልቶ ሊያገኝ አይችልም ዛሬ ነበር ምክንያቱም የእኛ ዐ ካሊበር መምታት የሚችለው አሳቸው በህይወት የሉም ስለ አሟሟታቸው የተለያዩ እስከተወሰነ ርቀት ብቻ ስለሆነ በወቅቱ የነበረውን አንቅስቃሴ አስተያየቶች ይሠጣሉ አውነታውን ወደፊት ታሪክ ሊያወጣው ለበላይ ሪፖርት ስደረግሁ ቢቻል ቢኤም እንዲላክልን ወይም ይችላል መርከቦቹ ከመጡ ታንኮች ነዳጅ ሞልተው እንዲደርሱልን ጠየቅን ኮሎኔል ገክርስቶስ እኛ ከነበርንበት ቦታ በፄሊኮኘተር መጡና ቦታው አሸዋማ ስለነበር መኪናዎች እንደ ልብ የሚንቀሳቀሰበት እዚያ ቦታ ላይ ምን እንደምንሰራ ጠየቁኝ የደረሰኝ ትዕዛዝ ይሄ ሁኔታ አልነበረም የጠየቅነው ሊደርስልን አልቻለም ቢያንስ ቦታ መሆኑን ገለፅኩላቸው አንድ ሁለት ቢኤሞች ቢደርሱልን ኖሮ ብዙ ጉዳት ማድረስ ያ የምታየጡ አኮ የአልጌና ተረተር ነው ለጊዜው ከፊት በተቻለ ነበር እንደ አጋጣሚ ሆኖ አልተሳካም አንድ አራት ተ ሚታየ ን ገ ሼ ሽ ህለ እሻኙት ተከዬል አዛዢ በደረጃ አሳውቂ የሚሆኑ የጠላት መኪናዎች መብራታቸውን እያበሩ በቀጥታ ወደ አ ቃሮራ አቅጣጫ ተፈተለኩ ወደተባለው ሥፍራ ሄድኩ ግን የያዝናቸው ታንኮች ነዳጅ ጨርሰዋል ነዳጁ ያለው ከመርከቡ ላይ ነው ሻምበል ንጉሴን እ ዛፍዊ ወደኋሳ ገቡ በማግስቱ ግብሩኃይል አዛዝ ስጠይቀው ነዳጁ ከ በታች መሆኑን ገለፀልኝ ድንገት ውጊያ ቢገጥመን እንኳን አጉል እንሆናለን አልኩና እሱ ወደኋላ አንዲቀር አደረግሁ በሌላ በኩል ደግሞ የቢኤም መድፎቻችን በአሸዋ ማጥቃቱን ከሜዳ ወደ ጉብታማ በታ ልንቀጥል ነው በቀጥታ ከባህር ጠለል ወደ ዳገት ወጣን እንደደረስንም ውጊያ ገጠመን ስለተያዙ እንደ ልብ መንቀሳቀስ አልቻልንም ነበር ተ ይዋል ኛ ሻለቃ ነው ውጊያው ሳይ እንዲገባ የተደረገው ብረትለበሶቻችንን ይዘን እንትስቅሰ ጀመርን ጠደፊት የአዛዣች መለዋወጥ አስፈላጊ መሆኑን የበላይ ስላመነበት የቀድሞ ር ሽ ክር አዛዣችን ኮሎኔል ብርሃኑ ተቀይረው የዐኛ ክፍሉጦር አዛዥ ግብረፅ ማዘገ ገታ ዐ ዛጡ መሠወር ራሪ ይሉ ማዘዣ ቦታ ከሚሆነው ሥፍራ ላይ የጠላት አንዲሆኑ ተወሰነ የኛ ብርጌድ አዛዥ ደግሞ ኮሎኔል ሰሙንጉስ መሜዎች ከጉብታ ላይ ሆነው ተኩስ ከፈቴብን አካባቢው ሜዳግ ነዋል ውጊያው በጣም ከባድ ሆነ መነቃነቅ አልተቻለም ቦታ ስለነበረ በብረት ለበሶቹ ተኩስ ተቆጣጥረን ከአካባቢጡ ጠላት ጋራው እንዳይያዝበት አጥብቆ ይዋጋል እኛም ጋራውን አባረርናቸው አቅም ስላልነበራቸው ወዲያው ሸሽተው ስለሄዱ ከ መ በየመሽቭ ስ መ ሃሳ ነሽ ለመያዝ እንታገላለን ግን አልቻልንም ጠላት ያለ የሌለ ኃይሉን ቦታውን ለመያዝ ቻልን የነበረውን አነስተኛ ውጊያ አስወግደን ነበር እዚያ ቦታ ላይ አሰባስቦ የገጠመን አንደምንም ፈፈ ቋቓፎጹጤ የ ን ቨ ግ ጭመ። ንንንትቅኑፒ ና ሬፍ ይዬ ሎሙ መ ንሽ ጋጉሙ ፌዴ ከሜዳው ላይ ያለውን ተረተራማ ቦታ ያዝንና አዳር አዚያው ሆነ መጥቶ መቀመጥ አይችልም ጊዜ ይወስድበታል ስንት ኛ ክፍለጦር በእግሩ ተገዞ በእለቱ ሊደርስ አልቻለም ፅኛና መስዋዕትነት ከተከፈለ በኋላ ጠላትም የዚያን ቦታ ጠቀሜታ ኛ ብርጌዶች ደግሞ መርሳተክላይ ደርስዋል ግን ማዕበሉ ስለተገነዘበ ቦታውን ቀድሞ ያዘው ዘግይቶ የተደረገው ሙከራ አላስጠጋ ስላላቸው ከመርከብ ሊወርዱ አልቻሉም ኛና ኛ ሳይሳካ ቀረ እንዲህ አይነት ወታደራዊ ስህተቶች ይፈፀሙ ነበር ብርጌዶችና ምድረነኩ ጀልባ ላይ የተጫኑት የነዳጅ ቦቴዎች ይህም በመሆነ ከማጥቃት ደረጀ ወደ መከላከል ለመመለስ በወቅቱ ደርሰው ከእኛ ጎን ቢገቡ ናሮ ኛ ክፍለ ጦርም በወቅቱ ተገደድን ታቢ አቅጣጫ ቢደርስ ኖሮ የአልጌና ጦርነት ፍጻሜው እዚያ ላይ በከረን ግንባር መሣሊት ያለው የወገን ጦር ናቅፋ በር ደረሰ በሆነ ነበር ዋና ግንባሮች የሆኑት አልጌናና ናቅፋ ሆኑ የናቅፋንም ጦርነት የጊዜንና የቦታን ጉዳይ አንድ ላይ ለማቀናጀት አልተቻለም መግፋት ስላልተቻለ በሁለቱም በኩል መከላከል ተደረገ አልፎ የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ በዚህ አካባቢ በሚገባበት ጊዜ የጠላት አልፎ የህብረት ዘመቻዎች ይደረጉ ነበር ለምሳሌ ናቅፋ ኃይል በዚሁ በእኛ ግንባር በኩል ያለው ብቻ ነው በግራም ሆነ የጠላት ውጊያ ከተከፈተ ኃይል እንዳይቀንስ እኛም በአካባቢው ሌላ በስተቀኝም አልነበረም ኛ ክፍለጦር ደግሞ ሲመጣ ያዝ ውጊያ እንድንከፍት የበላይ መመሪያ ያዛል በዚህ ዓይነት ሁኔታ የተባለውን ተረተር ይኮ ስለነበር ከበላይ በተሰጠው አመራር ግን ትዝ ይለኛል መጋቢት ዓም ናቅፋ ላይ ድንገት ጠላት ቦታው እሱ ስላልሆነ ወደኋላ እንዲመጣ ተደረገ የያዘው ግን ወደ ውጊያ ከፈተ እኛ በአስቸኳይ በማግስቱ በፊት ለፊታችን ጠላት ይዞታ የነበረውን መሬት ነው እዚህ ላይ ስህተት ባይፈጠር እንድናጠቃ ትዕዛዝ ተሰስጠን ሊሳካ ግን አልቻለም የሚያሳዝን ናሮ በቀድሞው ቦታ ላይ ሆኖ መንገድ በመዝጋትና ከስሩ ነገር ቢኖር ግብረኃይሉ የማይሆን ትፅዛዝ በመስጠቱ ከፍተኛ የነበረውን የጠላትን ተሽከርካሪ ሊያይ ይችል ነበር ወይም መስዋዕትነት ከፍለን አንድ ቦታ ላይ ከደረስን በኋላ ያንን ጋራ መንደርደሪያ ሊሆነው በሚችል አቋም ላይ መገኘት በቻለ ነበር ቧጠህ ውጣ ማለት አስቸጋሪና እንደዚሁ በከንቱ የሰው ኃይልን አሁን በማግስቱ ኛ ኛና ዐኛ ብርጌዶች ደረሱና ውጊያ ማስጨረስ ነው ተከፈተ ጠላትም ዛይሉን አሰባስቦ ማይሚዶን ለቆ ሲወጣ የእኔ ሻለቃ እንዲያጠቃ የተደረገው በሁለት ጉብታማ ማይሚዶ የነበሩት የጠላት ኛና ዐኛ ብርጌዶች ሌሊቱን ሲጓዙ መሬቶች መካከል የነበረች አንዲት አነስተኛ መሬትን ሲሆን አድረው እንቅስቃሴያችን እንዲገታ አደረገ በስተቀኝ በኩል ካታር በእውነት ህሊና ላለው ሰው በሁለት ከፍ ያሉ መሬቶች መካከል የሚባል ገዢ መሬት አስለ የፊት ለፊት ውጊያ ለእኛ የሚጠቅመን ያውም በወገን ያልተያዙ አነስተኛ ቦታዎችን አጥቃ ማለት ያ ጦር ነገር ስላልነበረ ካታርን የመሰለ ትልቁን ገዢ መሬት መያዝ እንዲያልቅ ከመፍረድ ውጪ የተለየ ሊሆን አይችልም የግብረ ወሳኝና ስልታዊ ጠቀሜታ አንዳሰው ለግብረኃይል አዛዢ በግሌ አሳወቀሁ ምክንያቱም ከጋራው በስተጀርባ የመድፍና የታንክ ኃይሉ አዛኝ አእምሮ ምን እንዳሰበ ለማወቅ አዳጋች ነው ትዕዛዙ በብርጌድ አዛዝ በኩል ጥዋት ሲደርሰኝ ምን ወታደራዊ ጠቃሜታ ሜካናይዝድ ስለሆንን ጠላት የራሱን እግረኛ ነቅሎ ከፊት ለፊታችን መልስ ግን የአለቃዬ ትፅዛዝ ነው የሚል ብቻ ነው ምንም ቪሚስጢሚጢሚጢሚ ሙ ፉኦጭፎ ኃ ፁኤ ጩኸት ይሰማል ሁለተኛ ደግሞ በዚያ በኩል ብንሰብር እኛ ናሮት ነው ይህንን ቦታ የምናጠቃው ብዬ ብጠይቅ የተስጠኝ ሥሥ መ መ መ ማድረግ አልተቻለም በዚህ ዓይነት ሁኔታ ያለን እድል ታንኮቻችንንና ብረት ለበሶቻችንን አሰልፈን ሁለቱን ከፍተኛ መሬቶች ወጥረን በተኩስ መያዝና በመድፍ ጭስ ጋርደን መዋጋት ብቻ ነው ይህ ውጊያ እንደማይሆን ስለማውቀው ለውጊያ ያስገባሁት አንድ የመቶ ጦር ብቻ ነበር የወገን ጦር ሰብሮ ገብቶ መሬቱ ላይ ወጣ አኛ በጭስ ለመጋረድ የሞከርነው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ስለሆነ ዘላቂ ውጤት ሊያስገኝ አልቻለም ወደፊት ለመሄድም አልተቻለም ወደፊት መግባትም ሆነ መላቀቅ አስቸጋሪ ነው የጠላት ጥይት እንደበረዶ ከላይ ይወርድባቸዋል ሁኔታው በጣም አናደደኝ ከነበርኩበት ቦታ ብረትለበሶችና ታንኮችን አስጠግቼ ቀስ ብላችሁ ለመላቀቅ ሞክሩ በማለት የቅርብ የተኩስ ድጋፍ ብንሰጥም አልሆነም ያ ጦር አዚያ ቦታ ላይ ተደመሰሰ ጠላት መልሶ ያንን ቦታ ሲቆጣጠር በአውሮኘላንና በመድፍ ቦታው ላይ የሰፈረውን የጠላት ጦር መታነው በዚህ ሂደት ውስጥ አንድ ይዘናት የነበረች አነስተኛ ጉብታማ መሬት ላይ ቆሜ በመነዕር ስመለከት አንድ የሆነ ነገር ቀፈፈኝ። በዚህ በኛው ምድብ ከናቅፋ የፄድነው መኮንኖች ኃላፊነታችን ከፍተኛ ነው አሥመራ አንደገባን ዘመቻ መምሪያ ሪፖርት አደረግን በበነጋው ትምህርቱ እንደሚጀመር ተነገረን አሄ ቤተሰቤ አሥመራ ከተማ ስለነበር ወደዚያው ሄድኩ ለሌሎችም ማረፊያ ቦታ ተዘጋጀላቸው ከንጋቱ ሰዓት ገደማ ሲሆን በር ተንኳኳ ተነስቼ ስከፍት ሰላምታ ከሰጡኝ በኋላ «ከዘመቻ መምሪያ ነው የተላክነው አውሮኘላን ማረፊያ ይፈለጋሉናቅፋ ውጊያ ተከፍቷል አሉኝ በግንባሩ ጥሩ የመከላከያ ይዞታ የነበረው ኛ ብርጌድ ለረዥም ጊዜ በመከላከል ላይ ስለቆየ ትንሽ አረፍ ይበል ተብሎ ወጥቶ ተጠባባቂ ኃይል ነበር ከኛ ለ ደግሞ ኛ ብርጌድ እንደዚሁ ተጠባባቂ ሆኗል እነዚህ ሁለቱ ብርጌዶች በጣም ጠንካራ ብርጌዶች ናቸው ያን ጊዜ ቅልፍት ከከረን ሲመጣ ሁለት ብርጌድ ወጥቶ ነው አጅቦና አስሶ እ ንንን ሙመኡ የሚያመጣው አሁን እነዚህ ሁለት ብርጌዶች ለቅልፊት ከወጡ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው ጠላት ውጊያ የከፈተው የጠላት ጦር ግዝግዛ ከሚባል ሥፍራ ላይ ፈንጂ በብዛት ጠምዷል እንደገና በኩብኩብና በአፋአበት መካከል እንደዚሁ በብዛት ፈንጂ ጠቅጥቋል ልክ ደግሞ እነዚያ ብርቱ ብርቱ ሰዎች ለሴሚናር አሥመራ የፄዱበትን ወቅት ጠብቀው ነው ጦርነት የከፈቱት ጠላት ሰብሮ የገባው በማኦ ወንዝ ሽለቆ በኩል ኛ ሚሊሺያ ብርጌድ በተባለው አቅጣጫ ነው ብርጌዱ ደግሞ ሚሊሽያ ሰለሆነ መደበኛ ደመወዝ ስለማይከፈለው ሞራሉ የተነካ ነው አዛዣቸው ኮሎኔል ደስታ ይባላሉ በጣም ጠንካራ መኮንን ናቸው እሳቸውም ከኛው ምድብ ጋር ለትምህርት አሥመራ ፄደዋል በጥዋት ወደ ግንባር የሚላክ ጦር ነበር ሰውና ቦምብ በአውሮኘላን ላይ በአንድነት አይጫንም የኛ ብርጌድ አዛሻ ጀኔራል እርቅይሁን ያን ጊዜ ሻለቃ አና እኔ በዚያኑ ቀን ከቦምብ ጋር ተጭነን በጥዋት ተነስተን ፄድን ሌሎቹ ሌላ ሄፄሊኮኘተር እንዲጠብቁ ተደረገ ልክ እንደደረስን ጦሩ በግራ በኩል እየለቀቀ ነበር እንደምንም ብዬ ወደ እኛ ማዘዣ ጣቢያ ልወጣ ስል ካሊበር አላስወጣኝ አለ ትዝ ይለኛል ፃምላ አለቃ ጎበዜ የሚባል አንድ አየር ወለድ ሹፌር ነበር እንደምንም አደረሰኝ በዚያን ወቅት ኮሎኔል ቁምላቸውን አገኘኋቸው ታንኮቹ ያሉበትን ቦታ ጠየቅሁና አሳዩኝ ታንኮቹ ገና አልወጡም የኛ ግብረኃይል ድርጅት ካለበት ቦታ ሆነው የተኩስ ድጋፍ እንዲሰጡና ታንኮቹ ተቆርጠው እንዳይቀሩ ወደ ታች እንዲወርዱ አደረግሁ ግምቴ ጥሩ ነበር በዚያ ያሉትን ገዢ መሬቶች ይዘን መዋጋት መርን ጦሩ ውጊያው ሌሊት ስለተነሳበት ምንም ማድረግ ሺ ሩኢሓፈዚሒሥፎ መ ህክ መ አልቻለም ቢሆንም ከዝቅተኛ ማዘዣ ጣቢያ ቀጥሎ ያለውን ዝቅተኛ መሬቶች ያበዘ አዚያ ላይ መዋደቅ ተጀመረ ለውጊያ የወጣው ቅልፍት ከደረሰ በስተግራ በኩል መልሶ ማጥቃት እናደርጋለን የሚል ተስፋ ነበረን አንድ ቀን ሙሉ አዚያ ላይ ዛፃይላችንን አጠናከርን ነገር ግን የጠላት ዛይል እየገፋ መጣ ጠላት ያለው ከገገር መሬት ላይ ነው የማደንቀው ግን የአኛ ሠራዊት በዚያ ዝቅተኛ መሬት ላይ ሆኖ ገትሮ በመያዙ ለሶስት ቀናት ያህል በዚያ ቦታ ላይ ተዋደቅን ለእጀባ የወጡት ኛና ኛ ብርጌዶች እንደገቡ ኛ ግብረኃይል ለግንባር ጠላት ማጥቃት ሰለጀመረና ግፊቱም እየተሳካለት ሰለፄደ ሁለቱም ብርጌዶች በዚያ አቅጣጫ አንዲገቡ የግብረኃይሉ አዛዥ ወሰነ በመጨረሻ ኃይላችን እየተመናመነ ሄዶ በዚያ በኩልም ጠላት እየገፋ መጣ የኛ ሠራዊት ናቅፋን ለቆ ወደ ኩብኩብ አፈገፈገ እኔ እስከ መጨረሻው ድረስ ነበርኩ ታንኮቹን ቦታ አስያዝኩኝ ወቅቱ ጨረቃ ነበር ሰው እኮ ከፊታችን የለም ታንከኞች በአርግጥም ከነሱ ፊት ቦታ ያስያዝኳቸውን ለማየት ስፄድ የጠላት ወገንን ድምፅ ብቻ ነበር የምስማው ከዚያ ወደ ኋላ መለስ ብለን ስናይ ድርጅቱም ሆነ ትጥቁ ሁሉ በሞላ ሜዳው ላይ ካለው ድንኳን ውስጥ ነው ትዝ ይለኛል ምክትል የመቶ አለቃ ካሳዬ የሚባል የኤርትራ ተወላጅ በግብረኃይሉ ድርጅት ውስጥ ነበር ከክርሱ ጋር ዶክተር ግርማ የሚባል ሲቪል ነበር ከእነሱ ጋር ሆነን በበርሜል ውኮቦ የነበረውን ነዳጅ አርከፈከፍንበት ጠላት እንዳያገኘው ታንኮቹን ወደ ኋላ ስበን በታንኮቹ መትተን አቃጠልነውጦው እኛ ብቻ ነን አሉኝ ኬክ ከዚያ በኋላ የነበረው ሁኔታ በጣም አስቸጋሪ ሆነ ወደኋላ ገፍተን ወደ ኩብኩብ እያፈገፈግን ስንሄድ ግራና ቀኙን ከተራራው ላይ የወጣ ጠላት በተለይም በስተግራ በኩል ያለው የጥይት ዶፍ አወረደብን እኛም አፀፋ መልስ ሰጠን ለጥቂት ጊዜ ግንኙነት ካደረግን በኋላ ተቋረጠ የንኡስ ግብረኃይሉ አዛዥ እኔ በህይወት ያለሁ አልመሰላቸውም አጠገባቸው መሆን ነበረብኝ ቦታ አስይዛለሁ ብዩ ከላይ ወደ ታች እንደወረድኩ ነው ይህ ሁኔታ ሊከሰት የቻለውወ ከቀትር በኋላ ወደ ሰዓት ተኩል ገደማ ሲሆን ኩብኩብ ገባን ቀደም ብሎ የገባውንም ጦር አዛ ቦታ አስይዘውት ነበር በማግስቱ አውሮኘላን ጠየቅን ተሰናክለው የቀሩ ብዙ መኪናዎች ነበሩ የኛ አውሮኘላኖች እንዲመቷቸው ተደረገ ገሚሱንም ጠላት ወስዲቸዋል በአውነት የናቅፋ መለቀቅ የራሱ የሆነ አሻጥር ነበረበት በሴሚናር ሰበብ ጠንካራ ኃይሎች የነበሩት እንዲወጡ መደረጉና አላስፈላጊ ሁኔታ መፈጠሩ ሆን ተብሎ የተሠራ ደባ ነው በሌላ በኩል ደግሞ መደበኛ ሠራዊቱ ደመወዝ እየተከፈለው በዚያ ቦታ ላይ በአመዛኙ ሚሊሺያ ለሆነው ሠራዊት ደረቅ ቀለብ ብቻ መስጠቱ ይህም ራሱ ለውድቀቱ ምክንያት ሆኗል የመደበኛውም ሆነ ሚሊሽያው ሠራዊት የተሰለፉት ለአንድ ዓላማ ነው በእርግጥ የሚሊሽያው ወደ ጦር ግንባር የተላከው ለከጭር ጊዜ ነው የወጣውም በኪስ ገንዘብ ብቻ ነበር በኋላ ግን ጦርነቱ እየተራዘመ ሲፄድ ሚሊሽያው መተዳደሪያው የሆነውን ግብርና ትቶ ነው ጦር ሜዳ የቀረው ቢያንስ እንደ መደበኛው ሠራዊት ደመወዝ ተከፍሎት ቤተሰቡን መርዳት ይኖርበታል የየየ በዚህ ላይ ደግሞ የቤተሰብ ናፍቆት አለበት በዚህ ሁሉ ምክንያት ሚሊሽያው ይበሳጫል በአጠቃላይ የሚሊሽያው ሞራል መነካት ጉልህ ሆኖ ይታየኛል ይሄንንም ደግሞ ለበላይ አካል ጭምር አመልክተናል አንድ ጊዜ ዶር ጋጋ አንድ የህክምና ቡድን ይዘው መጠ ሁሉም ክፍሉጦሮች ህመምተኞች ናቸው ያሉዋቸውን እንዲልኩ ተደርጎ ሲመረመሩ አብዛኛዎቹ የመንፈስ ጭንቀት እንደነበረባቸው ተረጋግጧል ለዚህም መንስኤው የቤተሰብ ችግርና ናፍቆት ነው በዚህም ገዳይ ላይ አስተዳደራዊ መፍትሄፄ እንዲስጥ የህክምና ቡድኑ ሪፖርት አቅርቧል በዚህ ላይ የአጭር ጊዜ ፈቃድ እንኳን ተሰጥቷቸው ቤተሰባቸውን እንዲጠይቁ አይደረግም ሌላው ቢቀር ከረን እንኳን ሄደው መንፈሳቸውን አዝናንተው እንዲመለሱ አይደረግም በወታደራዊ ሥርዓት ግንባር ላይ ያለ ሠራዊት ብዙ ጊዜ ሲቆይ ከዚያ አካባቢ ወጣ ማለት አለበት ይህ ከግንዛቤ ውስጥ ባለመግባቱ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል የአስተዳደር ችግር ያመጣው ጫና የመንፈስ ልልነትን ፈጥራል ይሄ ነበር መሠረታዊ ችግሩ አቅም የፈቀደው እንክብካቤና ትኩረት ቢደረግለት ኖሮ ምን ያህል ሞራሉ በጠነከረ ነበር ግን አልሆነም ሚሊሽያውን በአግባቡ ልንይዘው አልሞከርንም ለዚህ ነው ሞራሉ በቀላሉ ሊሰበር የቻለው መንግስት ወይም የበላይ አካል ይህንን ችግር ለመፍታት ወኔውም ድፍረቱም አልነበራቸውም ነገር ግን ሁሉም ከተበላሽና ካለቀለት በኋላ ለሚሊሽያው ደመወዝ ለመስጠት ተሞክራል ነገሮች ሁልጊዜ ከተበላሹና አመዕ ተነሳስቶ ጥያቄ ሲቀርብ ብቻ ነው ችግሩን ለመፍታት የሚሞከረው ችግሮችን ለመፍታት የሚወሰደው የመፍትሄ እርምጃ በጊዜው ቢሆን ኖሮ ሁኔታዎች የተለዩ በሆኑ ነበር ለውድቀታችን አንደኛው ምክንያት ይሄ ነው ርር ኩብኩብ አመቺ ሥፍራ ስላልነበረ ሠራዊቱ ወደ አፍአበት ገባ በአጠቃላይ መከላከሉ አፍአበት ላይ እንዲሆን ተደረገ የኘሬዚዳንቱም የካሴት ንግግር ተልኮ ሠራዊቱ እንዲሰማው ሆነ ኛ ክፍለ ጦር የኛ ሆ ንኡስ ግብረኃይል በቀኝ ክንፍ በኩል ወደ መአይሚዶ እንዲጓዝ ተደረገ ከከረን ወደ አፍአበት ስንቅና ትጥቅ እንዳያልፍ ጠላት ከኋላም አልፎ ግዝግዛን ዘግቶታል ስለዚህ በመርሳጉልቡብ በኩል መምጣት አለበት ስለተባለ እኛ መአይሚዶ ሄደን መከላከያውን አጠንክረን ያዝን ከእኛ ቀደም ሲል በኮሎኔል መንገሻ ታደሰ የሚመራው ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ይኮት ነበር ኮሎኔል መንገሻ ታደሰ ኛ ብርጌድ ውስጥ በኛ ታንክ ሻለቃ የኛ ሻምበል አዛዥ ሆነው ሲሠሩ አውቃቸዋለሁ መኮንኑ ግልፅና ጥሩ ወታደር ናቸው በለውጥ ያምናሉ በ ዓም ለውጡ ሲቀጣጠል ሐረር የኛ ቃሺ አዛዥ ሆነው ትልቁን ሚና ተጫውተው ወደ አዲስ አበባ በደርግ አባልነት ተልከውም ነበር መኮንኑ የፕሬዚዱንቱም ኮርስ ናቸው ፈጣንና ሀቀኛ ስለነበሩ ለእነ አጅሬዎች የማይመቹ ስለሆኑ በጥዋቱ ከዚያ ተባረው እንደ ሥራቸው የሚረባ ዕድገት ሳያገኙ በረሃ ውስጥ ከክፍል ክፍል ተንከራተዋል በእነርሱ ቋንቋ ጨቅጫቃ ናቸው ቢሏቸውም እርሳቸው ግን ትክክለኛ መሆናቸውን የምናውቅ እንመሰክራለን መርሣጉልበብ ላይ ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ እንዲቀመጥ ተደረገ ማንኛውም ስንቅና ትጥቅ በላንዲንግ ክራፍት ይጓጓዛል ግዝግዛ ላይ የነበረው የጠላት ጦር አዚያ መቀመጥ ስላልቻለ ለቆ ወጣ የከረን መንገድም ተከፈተ እኔ እዚያው እያለሁ መከላከያውን ካደራጀን በኋላ ቅኝት ጀመርን በዚያን ወቅት ለአጭር ጊዜ የዘመቻ መኮንን ሆነው ሰሜን አዝ የመጡት ጀኔራል መስፍን ገብረቃል ናቸው ቅኝት ወጥቶ የጠላት መሣሪያ ይዞ የመጣ ወታደር መሾም አለበት ብለን ጀኔራሉን አስፈቀድን ቅኝት እያደረግን ቀስ ብለን ከመአይሚዶ ጉዚችንን ወደፊት ቀጠልን ጠላትን እየመታን ቦታ ማስለቀቅና ወደፊት መራመድ ጀመርን በአፍአበት ግንባርም ኛ ክፍለጦር ተመሳሳይ እርምጃ ወሰደ ቅኝት ወጥተው የጠላት መሣሪያ ይዘው ለመጡት ሹመት መስጠቱ ሲጀመር የሠራዊቱ ሞራል ከፍ እያለ መምጣትና ወደ ጥሩ ደረጃ መሸጋገር ጀመረ በዚህ ላይ እንዳለን እኔ ወደ ቀድሞዋ ሶቪዬት ህብረት ለትምህርት እንድሄድ ተመረጥኩ ጀኔራል ቁምላቸው ደጀኔም በሹመት ወደ ሌላ ክፍል እንዲዛወሩ ተደረገ ጀኔራል ቁምላቸው መንገድ ላይ ብረት ለበሱ ከመንገድ ወጥቶ ተመታና ጀርባቸው ላይ አደጋ ደረሰባቸው እንዳጋጣሚ አደጋው የደረሰው እሳቸው ወደኛ ሲመጡ እኛ ደግሞ ወደሳቸው ስንሄድ ነው በወቅቱ ደርሼ ያነሳኋቸውም እኔ ነበርኩ አደጋው ሲደርስ ጊዜው ከሰዓት በኋላ ነው እዚያው ቦታ ላይ እያለሁ ፄሊኮኘተር እንዲላክልን ጠየቅሁ ትንሽ ጉም ቢጤ ይታይ ስለነበር በባህሩ በኩል ዝቅ ብሎና መሬቱን ይዞ በመርሳ ጉልቡብ በኩል እንዲመጣ ለፓይለቱ መልዕክት አስተላለፍኩ ፓይለቱ በጣም ጎበዝ ነው እንደምንም ብሎ መጣ ጀኔራል ቁምላቸውም አሥመራ ደርሰው ሆስፒታል ገቡ ለትምህርት ወደ ሶቪዬት ህብረት ለመፄድ መመረጤን ጀኔራል አብዱላ ኡመር ተቃወመ ለዘመቻው ሰው ስለሌለኝ አልልክም አለሉ የእኔ ክፍለጦር አዛዥ ጀኔራል ኃይሉ በራወርቅም ሰው ስለሌለኝ አርሱን የሚመጥን ሰው ይሰጠኝ ብለው ርር ሥሩ ርክ ጥያቄ አቀረቡ ለጊዜው ትንሽ ውጣ ውረድ ተፈጠረ እኔም ለጊዜው ተስፋ ቆረጥኩ «ካሁን በፊት ምፅዋ እያለሁ ትሄዳለህ ተብዬ ቀረሁ አሁን ደግሞ ይፄ ተፈጠረ የማትልኩኝ ከሆነ ለምን ትነግሩኛላችሁ። ግድየለም በመጀመሪያ ወደ ግንባር ይሂድና እዚያ እያለ ይሰጠዋል የሚል መልስ ተሰጠ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ በማግሥቱ ከርከበት እንድሄድ ተደረገ ጀኔራሉም ከእኔ ቀደም ብለው ቦታው ላይ ደርሰዋል የፖለቲካ ኃላፊው ደግሞ ሻለቃ ደጀኔ ወንድማገኘሁ የሚባሉ የደርግ አባል ናቸው ከእሳቸውም ጋር ተዋወቅን ጀኔራል ቁምላቸው ደጀኔ ሁሉንም ነገር አንድ በአንድ አስረዱኝ በተለይ ሁለቱን ብርጌዶች አዋህጄ አንድ ጠንካራ ብርጌድ እንዳደራጅ መመሪያ ተሰጠኝ የሁለቱንም ብርጌዶች ቫለቃ አዛዥችና ሻምበል አዛገፐች ሰብሰባ ጠራሁ በአዲስ መልክ ስለሚደራጀው ኃይል ዓላማና ወደ አንድ ጠንካራ ኃይልም ተጠቃሎ ስለሚዋቀርበት ሁኔታ ገለጻ አደረግሁላቸው ከዚያም በመቀጠል በሁለቱ ብርጌዶች ውስጥ ያለውን የሰው ኃይል አቀረብኩላቸው ኃይሉ ብዙ ስለሆነ ጥሩ ተዋጊ ተኳሽ ሾፌር በአጠቃላይ ጥሩ ባለሙያ ነው የምትሉትን ከሁለቱም ብርጌዶች ለይታችሁ መዝግቡ ደካማና ዲስኘሊን ይጎድለዋል የምትሉትንም ለይታችሁ እወቁ ከቪያም በመቀጠል ደግማችሁና ደጋግማችሁ አጣሩና የጋራ ውይይትም አካዚዱ» የሚል መመሪያ ሰጠሁ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ማንኛውም ሥራ ሁሉ ተከናወነ ጠንካራ አባላትንም ማግኘት ተቻለ ይህ የሆነው ጥር ቀን ዓም ነበር ይህንን ባጠናቀቅን በማግሥቱ የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ አግረኛውን ኛ ሻለቃ የኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ እግረኛ ታታ ንን አሱሙሙውሲ ሙፌሙኡ አባላትን ኛ መካናይዝድ ሻለቃ በማድረግ ቀሪውን እግረኛ ኛ ሻለቃ አድርገን አቋቋምን ከዚያ በኋላ ከታንከኛውም ከመድፈኛ ውና ከአየር መቃወሚያ ከቃዎችና ከተዋጊ መሐንዲሶችም ብቃት ያላቸውን ከመደብን በኋላ መሣሪያውንና ተሽከርካሪዎችን በበቂ ሁኔታ አዘጋጀን በቀጣዩ እርስ በርስ እንዲተዋወቁ ካደረግን በኋላ ባለችን ቀናት ውስጥ ሥልጠና ጀመርን ለጦሩም መመሪያ ተስጠ በዚህ ዓይነት መልኩ ጦሩን ደህና አድርገን ለማስተካከል ቻልን ወቅቱና ጊዜው ሲደርስ ፕሬዚዳንቱ መጥተው ገብኝት አደረጉና መመሪያም ሰጡ እኔ የምመራው ጦር እንዲገባ የተሰጠው አቅጣጫ በሱዳን ጠረፍ ዐ ኪሜ ገደማ በሳላ በር በኩል ሲሆን ኛ ተራራ ክፍለ ጦር በኩር በኩል ፄዶ እንዲያጠቃ ኛ ክፍለ ጦር ደግሞ በሳታ በኩል አድርጎ እንዲያጠቃ ነበር ኛ ተራራ ክፍለጦር ገና አዲስና ከማሠልጠኛ ማዕከል ስለመጣ ኤርትራ ውስጥ የውጊያ ልምድ የለውም ኮዳቸውም እንኳን የሶቪዬቶቹ ትንንሽ ኮዳዎች ናቸው በኩር በኩል እንዲሄዱ ተደረገ ርቀቱና ሀሩሩ ከባድ ነው እንደምንም ብለው ወደ ጠላት ምሽግ ተቃረቡ እንዳጋጣሚ ሆኖ ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው ይህንን ሠራዊት የፈታው ውዛፃ ጥም እንደነበር ከውጊያው በኋላ ከቀረበው ሪፖርት ተረድቼአለሁ ሰንጥቅ የመጀመሪያ ግዳጁን በሻለቃ ደረጃ በድል ተወጥቶ ሲመለስ ኛ ክፍለጦር ሳታን አልፎ ሄዲል እኔ የምመራው ጦር ደግሞ በስተግራ በኩል ሁምቦል ወንዝን ተሻግሮ በረሃውን ተያይዞታል ከአሸዋና ጥቃቅን የበረሃ ቁጥቋጦዎች በስተቀር ጎላ ብሎ የሚታይ ምንም ነገር የለም ቀደም ሲል በተደረጉ ውጊያዎች ይመስለኛል የመቃብር ቦታዎች ብቻ ይታያሉ አካባቢው ጦርነት የተካሄደበት ቦታ መሆኑ ያስታውቃል ከጀብፃ ጦር ወደ እኛ ከተመለሰ አንድ መንገድ መሪ እንደሰማነው ጀብዛና አልዋህዳ የተጋደሉበት ሥፍራ እንደሆነ አውግቶናል በቅርቡም ብዛፃና ሻዕቢያ ተዋግተው በተለይም ሻዕቢያ ጀብፃን የደመሰሰበት ቦታ መሆኑን ነገረን ብዙ ሰዎች እንዳለቁ የመንገድ መሪው ቢነግረንም አካባቢው ያስታውቃል ይፄ ብቻ ሳይሆን በዚያ ሥፍራ በኛውና በ መቶ ክፍለ ዘመን ውጊያዎች የተካሄዱበት ሥፍራ እንደሆነም ይነገራል ርዴ ያም ሆነ ይህ የተሰጠንን ግዳጅ ለመወጣት ጉዞዋችንን ቀጥለን ሳላበር ልንደርስ ዐ ኪሎ ሜትር ገደማ ሲቀረን በመነጽር ስመለከት በሩ ላይ ጠላት ቆፍሮ መሽጓል አካባቢው የጠላት ወረዳ በመሆኑ መመሸጉ ባይገርመንም የእኛ ንቅናቄ ላይ ሻጥር አለበትተብሎ ለሚነገረው ጉዳይ አንዱ ማስረጃችን ሊሆን ችሏል ምክንያቱም መሽጎ የተከማቸው የጠላት ጦር ከርከበትና ሳታ ላይ ቢሆን ባላስገረመን ነበር የሚያስገርመው ግን ሻዕቢያ መረጃ ካላገኘ በስተቀር በዚያ ርቀትበዚያ በር ላይ ምሽግ አዘጋጅቶ መጠበቅ አይቻለውም ለዚህም ነው አስተማማኝ መረጃ እንደተሰጠው አመልካች ነው ያልነው መረጃዎች ከማዕከል አንስቶ በብዙ መልካቸው ሊወጡ ይችላሉ አንድም እዚያው ከእኛ ጋር ዘመቻ መምሪያ የሚሠሩ ሰዎች መረጃ እንደሚያቀብሉ ይጠረጠራሉ የውጭ አገር አማካሪዎችም ቢሆኑ እምነት የሚጣልባቸው ሊሆኑ አይችሉም ሻዕቢያ ደግም ለሚፈልገው መረጃ የተፈለገውን ያህል ገንዘብ በሰጥ ደንታው አይደለም ምክንያቱም የአንድ ውጊያ ተግባራዊ ዕቅድ የሚመሠረትባቸው አንዱና ዋነኛው በጠላት ሁኔታ ላይ ያተኮረ መረጃ ሲገኝ ነው ሁልጊዜ የመረጃ መሹለኪያ ቀዳዳዎች ከውስጥም ከውጭም ከአለቃም ከጭፍራም ከደግነትም ሆነ ከክፋት ከወገንተኝነትም ሆነ ከጠላትነት ወዘተርፈ በመሆናቸው የመጠራጠር ባህርይ እያዳበርኩ ፄጃለሁ። » ሲሉ ጠየቁኝ ጦሩ የተቋቋመው ለጦርነት ነው እኔም የመጣሁት ለዚሁ ሲባል ነው ጦሩ እዚህ ከተማ ውስጥ እንዲቀመጥ ከተደረገ ደግሞ አንዳንድ የማይፈለጉ ሁኔታዎች ሊከሰቱ ይችላሉ» ስላቸው ጀኔራሉ ለጊዜው ተቆጠኝ «በከንተ ሳይሆን በበላይ አካል የሚሰጥ ውላኔ ነው አሉኝ የበላይ መኮንን ስለነበሩ ለጊዜው ዝም አልኩ ኋላ ግን አውራጃ አስተዳዳሪውን ካነጋገሩ በኋላ ወደ አውሮኘላን ሲገቡ ጠሩኝና «አንተን ለማበሳጨት ስል አይደለምና አትቸኩል ሁን እንደተባልከው ሁን አሉኝና ጉዞዋቸውን ቀጠሉ እኔም ጦሩን የማሰልጠኑን ተግባሬን ቀጠልኩ በዚያ ወቅት የቀይ ኮከብ ዘመቻ የሚካፄድበት ጊዜ ነበር የዚያ ዘመቻ አሳዛኝ ነገር ቢኖር በመጀመሪያ ጠላት ሙሉ በሙሉ መረጃዎችን አግኝቷል ቀደም ሲል ወደ ሳላ በር ስንፄድ የተዘጋጀውን ምሽግ ካየሁት በኋላ የሆነ ደባ እንዳለበት ቀደም አድርጌ ገልጨዋለሁ ከዚህ በላይ ደግሞ የሚያሳዝነው የወገን ጦር የበላይ አለቆች ያቀዱት ጦርነት በሻዕቢያ ወንበዴዎች ላይ ብቻ ነበር ሌላ ተጨማሪ ኃይል ወይም ጠላት ይመጣል የሚል ግምት አልተወሰደም በወቅቱ ምንም እንኳን በናቅፋ ግንባር ባይኖርም ሁኔታውን ስከታተለው ወገን በጥሩ ሁኔታ አጥቅቶ እንዳውም ኛ ክፍለጦር ወደ ናቅፋ ኤርፖርት መግባት ጀምሯል በዚያን ጊዜ ነበር ተጨማሪ የጠላት ከ ብርጌድ በላይ ጦር የመጣው ጋታ ፌ ሔሒሔፌ ፌኢኢኡኢ የሚሆኑት ተማረኩ ጉዳት የደረሰባቸው ግን በርካታ ናቸው የስንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ በአዲስ መልክ ከተዋቀረ በኋላ የመጀመሪያ ዓይን መክፈቻ ግዳጅ በኛ መካናይዝድ ሻለቃ ተከፈተ በወቅቱ በተገኘው ድል አደራ የሚባል አንድ ኤርትራዊ የበታች ሹም ኋላ መኮንን እና ሌሎችም አንድ ሶስት ልጆች በፈጸሙት ጀብዱ የጀግና ሜዳልያ እንዲሰጣቸው ጽፌ ሽልማቱን አግኝተዋል ወደ ገደማ የሚሆኑትም የማዕረግ እድገት አግኝተዋል በጠላት ላይ የሰነዘሩት የተቀነባበረ ምት ስለነበረ አካባቢውን አጸዱት የተለቀቀውንም የወገን ጦር ይዞታ ከያኩና ካረጋጉ በኋላ ወደ አቆርዳት ተመለሱ ይህ ለእኛ ደግሞ የመጀመሪያው ድል ስለሆነ የደስታ ቴሌግራሙ ጎረፈልን አቆርዳት ያለውም ጦር ከአቆርዳት መግቢያ በር ላይ እኔና አስታፎቼ እንዲሁም ሠራዊቱ ተሰልፈን አበባ ጉንጉን አበርክተን ተቀበልናቸው በቀጥታ ወደተዘጋጀው ድንኳን ፄድን ድግሱ ከተበላና ከተጠጣ በኋላ የጦሩ ፉከራና ሽለላ ቀጠለ የሌሎችንም ወኔ ቀሰቀስሰው ከዚያ በኋላ ሥልጠናችንን ቀጠልን ጦሩ የበለጠ በሰለጠነ ቁጥር የበለጠ መስዋዕትነት ለመቀበል ዝግጁ ሆነ በዚህ ሁኔታ ላይ እንዳለን በአቆርዳትና በባሬንቱ መካከል ያለው መንገድ ዝግ በመሆኑ ባሬንቱ ለነበረው ጦር ቀለብ ይደርስ የነበረው በአውሮኘላን ነው በአውሮኘላን ማጓጓዝ ደግሞ በጣም ውድ ነው ስለዚህ ይቕ መንገድ መከፈት ስለነበረበት በወቅቱ በአሥመራ ዙሪያ ላለው የመክት ዕዝ ተደራቢ ስለነበርን ጀኔራል አብዱላሂ ኡመር መንገዱ እንዲከፈት ከአለንበት ድረስ በፄሊኮኘ ተር መጥተው ትፅዛዝ ሰጠኝ በመጀመሪያ ቅኝት አደረግንና እግረኛውን ጦር ቦታ አስያዝን ይሁን እንጂ መንገዱን አልተከተልንም የሻዕቢያም የጀብዛም የወገንም ፈንጂ ይኖራል የሜል መረጃ ስለደረስን በተቻለ መጠን ከመንገዱ ውጪ ጫካውንም ቁጥቋጦውንም በታንክ እየጨፈለቅን ተጓዝን ምርጫአልባ የሆነ ቦታ ሲያጋጥመን ደግሞ ፍተሻ በማካፄድ መንገዱን ይዘን እንጓዛለን ለማንኛውም መንገዱን በሙሉ በመዛንዲሶቻችን ደግመን ደጋግመን ፈተሽን ከኪያ በኋላ በፈንጅ ጠራጊ ተሽከርካሪ ላይ ሆነን ጉዞአችንን ቀጠልን አልፎ አልፎ ፈንጂ እየፈነዳ ፈንጅ ጠራጊውንና ታንኮቻችንን ይመታል በዚህ ዓይነት መልኩ በ ቀናት ውስጥ እስከ ባሬንቱ ድረስ ያለውን መንገድ ወጥረን በተቻለ መጠን የሚወጣውን ፈንጂ አውጥተን እንደምንም ብለን የመጀመሪያውን ቅልፊት ርበህዐሃ ለባፊንቱ ሕዝብ አስገባን የባሬንቱ ሕዝብም በጣም ተደሰተ የሰንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ ተወርዋሪ ሆኖ ቅኝት እያደረገ በወር ጊዜ ደግሞ ባሬንቱ ላለው ሠራዊት ቀለብ እያደረሰ ቀዋየ በ ዓም ቀኑና ወሩን አላስታውስም በትግራይ በኩል ኛና ኛ ክፍለጦሮች ከሽሬ ተነስተው አዲዳሮከአዲዳሮ አዲአገራይ ከአዲአገራይ ሽራሮ አድርገው የማጥቃት ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው ተንቀሳቀሱ ልክ አዲዳሮ ላይ ሲደርሱ ከናቅፋ የማያንስ ምሽግ ተሠርቶ ጠበቃቸው ዘመቻው ከመካፄዱ በፊት ገና ሲታቀድ ጠላት ያውቅ እንደነበር ሌላ ማስረጃ ማቅረብ አያስፈልግም ጠላትም የወገንን ጦር እንቅስቃሴ በመግታቱ የእኛ ግዳጅ ከኤርትራ ከቆርዳት ተነስተን ከጠላት ጀርባ በጥልቀት ገብተን ወደፊት መነቃነቅ ያቃተውን የወገን ጦር መደገፍ ነበር በአርግጥም ጠላት ሌላ ናቅፋ ነው የፈጠረውወ ለዚህም ነው ከጠላት ጀርባ የሚዘምት ሌላ ቆራጥ ጦር አስፈላጊ ሆኖ የተገኘው ጦሩ ከኤርትራ ተነስቶ ሽራሮ ዘምቶ ያንን አካባቢ ካስለቀቀ በኋላ ሦሥርሩሥዴጭራኗዉመጂመ ዴ ዴዴ ኤሙሙሙጨ ወደ አዲአገራይ ገብቶ በቀጥታ አዲዳሮን ከኋላ መምታት የሚችል ማን መሆን አለበት» ለሚለው በጠቅላይ መምሪያ ጥያቄና ፍላጐት በአንድ ድምፅ ሰንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ ተመረጠ ይህ አይነቱ ምርጫ ለእኔ ለአዛና ለምመራው ጦር በበላይ አለቆች ዘንድ ለወሳኝ ግዳጅ መመረጥ መታደል ነው ከማለት ውጭ ቃል አይገኝለትም ኛ ብርጌድ ቀደም ሲል በዐ ዓም ባሬንቱ ላይ መሬት ነክሶ ትልቅ ታሪክ የሠራ ጦር ከእኔ ጋር እንዲዘምት ዕቅድ ወጣ አቆርዳት ላይ እያለሁ በአስቸኳይ ባሬንቱ እንድገባ ትዕዛዝ ተሰጠኝ በጥዋት ማለዳ ተነስተን መንገድ ላይ ፈንጂ መኖሩን ማረጋገጥ ስላልተቻለን እያሰባበርን ሰዓት ሲሆን ባሬንቱ ገባን ከባሪያ መጎሎ እስከ ባሬንቱ ድረስ በዳገታማ መንገዱ ላይ ፈንጂዎች እንዲመረመሩ ትዕዛዝ ሰጠሁ ታቹን በተኸረሪት በኩል አድርገን ገባን ጠላትም በዚያ በኩል ስለማይጠብቀን ምንም ፈንጂ ሳይገጥመን ደረስን ባሬንቱ እንደደረስን መሰብሰቢያ ወረዳ ገባን ያን ጊዜ ኛና ሰንጥቅን የሚያስተባብሩት ኮሎኔል በቷላ ጀኔራል ነጋሽ ወልደየስ ነበሩ ከበላይ የተሰጠን ትፅዛዝ በቀጥታ ከባሬንቱ ተነስተን ወደ ቶኮምቢያ ከዚያ ወደ ሺላሎ ከሺላሎ ወደ ሽራሮ እንድንሄድ ነው አስከ ቶኮምቢያ ድረስ ያለው መሬት ገላጣ ስለነበረ ለመጓዝ ብዙም አልተቸገርንም ነገር ግን ከቶኮምቢያ ወደ ሺላሉ ስንሄድ በጣም ዳገታማ ነው በዚያ ሥፍራ ጠላት ቢኖር ኖሮ በምንም ዓይነት ያንን ቀጭንና ዳገታማ መንገድ አልፈን መጓዝ ባልተቻለን ነበር በታዘዝነው መሠረት ከባሬንቱ ተነስተን ቢንቢና ወረድን ከቢንቢና ወደ ኩሉኩ ከኩሉኩ ፎዴ ከሚባል ቦታ ስንደርስ በአሰሳ መልክ ሻለቃ ጦር የግራ ተረተሩን ይዞ ወደ ቶኮምቢያ እንዲሄድ አደረግን ወደ ቶኮምቢያ ስንቃረብ ገላጣ መሬት አገኘን ዴዴ ዴሙሙኢጨጹኡጤሜጫሙመጨ ዱሓ ና ጠላትም በቦታው አልነበረም ይኖራል የሚል ግምትም አልነበረንም ያለ ምንም ተቃውሞ ቦታውን ያዝነው ወደ ኪሎ ሜትር ገደማ አልፈን ወደ ሺላሎ ቀጠልን ሜዳማ ቦታ አገኘን ሜዳማ ቦታውን ወጣ እንዳልን መድፋችንን ጠመድንና ጋራውን በእግረኛ ተያያዝነው ገና ተረተሩን እንደተያያዝነው ግን ከጠላት ተቃውሞ ገጠመን የጠላት ጦር በግምት አንድ ሻለቃ ጦር ገደማ ይሆናል አሱንም መግፋት ጀመርነው ወደ ኪሎ ሜትር ገደማ ገፋነው መሬቱም ከፍ እያለ መጣ ታንኩንም መሣሪያውንም አስጠግተን መታነው ለሽላሎ ወደ ኪሎ ሜትር ገደማ ሲቀረን ከፍተኛ ገዢ መሬት ያዝን ከባድሜም አካባቢ ጠላት ይመጣሉ ብሎ ጠብቆን ነበር ቁርጡ ይሄፄ መሆኑን ሲያውቁት በባድሜ በኩል መረብ ወንዝን ሽጥ ለሸጥ ተከትለው መጡ እኛ የመጣነው ደግሞ ረዘም ባለው መንገድ ነው በጋ ስለሆነ ወንዙ ደረቅ ነው ጠላት ማታውኑ ገባ አሁን ተጨማሪ ጣቢያዎች መጨመራቸውን አወቅን እኛ የእነሱን ሬዲዮ እንጠልፍ ነበር የሰሜን እዝን የሚመሩት ሜጀር ጀኔራል ኃይለ ጊዮርጊስ ኃብተማርያም ሲሆኑ የመንጥር እዝ አዛዥ ደግሞ ሜጀር ጀኔራል ረጋሣ ጅማ ቦታው ላይ ተገኝተዋል በወቅቱ ሥውር ሬዲዮ ይዣለሁ ይሄ ነገር የማይሆን ነው በእኔ ሬዲዮ እሳቸውን ያናግራቸውና ሌላ ተለዋጭ ትዕዛዝ ይሰጠኝ እኔ ግን ሽራሮ መግባት እችላለሁ አልኳቸው «በየት በኩል ነው የምትገባው። ሱችቶችአሮ ናመ ከዚያ ጉዞዋችንን ወደ ደደቢት ስንቀጥል አንዳንድ የጠላት አስተባባሪዎች ከየመንደሩ እየሸሹ መውጣት ጀመሩ እኛ እዚያ ቦታ እንደርሳለን የሚል ግምት አልነበራቸውም አንዲት መኪናም ስትሸሽ የምታበነው አቧራ ከለለንና አመለጠችን እንጂ ልንመታት ተቃርበን ነበር መንገዱ የሚያልቀው ደደቢት ሲደርስ ነው ጠላት ድርጅቱን ለማሸሽ ወይም ለሰመደበቅ የሠራው ጥርጊያ መንገድ ነው ከፊት ብረትለበስ ቃፒ ቀጥሎ አንድ ታንከኛ የመቶና ሜካናይዝድ የመቶ አድርገን ነበር የምንሄደው ቃፒዎቹ የደደቢትን ዝቅተኛ መሬት ወረድ እንዳሉ ለካ ጠላት ዙሪያውን ባሉት ጉብታማ ቦታዎች በጠባቡ ደፈጣ ስላደረገ የመጀመሪያው ብረትለበስ ከመጨረሻው ጠርዝ ላይ እንደደረሰ ተኩስ ከፈቱበት ስንመለከት ዙሪያውን ድንጋይ ቆልለዋል ደግነቱ ታንኩ ከውስጥ አልገባም አንድ ሜካናይዝድ ሻምበል በስተቀኝ በኩል ከኋላ ያለው ሜካናይዝድ ሻምበል ደግሞ ወረደና ጠጋ ብሎ በስተግራ በኩል በእግረኛ እንዲያጠቃ አደረግን በጣም ምቹ ስለነበር የጠላት ጦር እንዳለ ጉዳት ደረሰበት ዐ ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ደደቢት በቁጥጥር ስር ዋለ የቃሺፒውን ብረት ለበስ ጎማዎች እንዳለ በጥይት በሳሱዋቸው እንዲያውም ትናንሽ ልጆች በብረት ለበሱ ላይ ቦምብ ለመወርወር ሲዘጋጁ የሁለተኛው ብረት ለበስ ተኳሽ ዝቅ አድርጎ ሲተኩስ የሁለቱንም እግሮች ቆረጣቸው እነሱም ይዘውት የነበረው ቦምብ በላያቸው ላይ ፈነዳ በዚህ ዓይነት ደደቢትን ከተቆጣጠርነው በኋላ ሁኔታውን ለበላይ ሪፖርት አደረግን እዚያው ያዙ የሚል ትዕዛዝ ተላለፈልን ትዕዛዙ ግን ስህተት ነበር ደደቢት ማለት ጭልፋ መሳይ ጎድጓዳ መሬት ናት ለእንደዚያ ያለ ኃይል ስለማይሆን ሁኔታው ያ መሆኑን ስንገነዘብ ክክክ ሽ ዴዴ የበላይ ትዕዛዝ ስለሆነ የዘመቻ መኮንኑንና የእኔን ብረት ለበሶች ታንኮችና ዙ አስቀርተን የቀረውን ብረትለበስና መድፍ በመሉ ወደ ማይኩሊ እንዲመለስ አደረግንና በሁለት አግረኛ ሻለቃ ብቻ ቦታውን ያዝነው ይህ ባይሆን ኖሮ ከባድ ውድቀት ይደርስብን ነበር በማግስቱ ዐ ኪሜ ዙሪያችንን ቅኝት ያደረግን ቢሆንም ምንም ነገር አላገኘንም በኛው ቀን ከበላይ አካል ጀኔራል አበበና ሌሎችም የኢሠፓ ፀዛፃፊዎችና ሲቪሎች ጭምር እንዲሁም አንዳንድ የክፍለ ሀገሩ ባለሥልጣኖች በሄሊኮኘተር መጡ «አሁን ያለንበት ሁኔታ አሳሳቢ ነው ስለዚህ ኪሜትር ገደማ ወደ ኋላ ብንሄድ ሜዳማ ቦታ አለ ትክክለኛው መንገድ ያለው በማይባሬ በኩል ስለሆነ ጊዜ ከምናባክን ወደ ማይባሬ ተመልሰን በማይባሬ በኩል ብንሄድ ይሻላል የሚል ፃሳብ አቀረብኩ «ጥሩ ነው ትዕዛዙ ነገ ይደርስዛልና ለጊዜው ግን እዚሁ አዳር አድርግ ተባልኩ ማታውኑ በየአቅጣጫው ያፈገፈገው ወደ ሁለት ብርጌድ ገደማ የሚሆን የጠላት ጦር ተሰባስቦ ሁለት እግረኛ ሻለቃ ብቻ በሆነው የኛ ጦር ላይ ውጊያ ቢከፍት አንደሚያዋጣው ተማምና አቅጣጫውን ወደ አኛ አሀረ ከፊት ለፊት ለደፈጣ የወጡ ልጆች ከሌሊቱ ዐ ሰዓት ገደማ ሲሆን ሪፖረት ማድረግ ጀመሩ ከፊት ለፊት እየተሳበ የሚመጣ ኮሽታ አለ ይላል አንደኛው ሌላውም ተመሳሳይ ቃል ያሰማል በዚህ ጊዜ ለደፈጣ የወጡት ወደ ውስጥ እንዲሳቡና ጦሩም በሞላ እንዲነቃ ተደረገ «ምንም ይሁን ምንም ልክ አጠገባችሁ ሲደርሱ ውጊያውን በቦምብ ጀምሩት አንድ ጥይት እንዳትተኩሰ» የሚል ትዕዛዝ ሰጠሁ እግዚአብሔር ሲረዳኝ ተጠባባቂ ጥይትና ቦምብ በየጓዱ በሳጥን በሳጥን እንዲወርድ አድርጌ ነበር ከሌሊቱ ዐ ሰዓት ላይ በስተቀኝ በኩል ከአንድ ከፍታማ አቅጣጫ ላይ ጠላት ውጊያ ከፈተብን ከዚያ በኋላ ዙሪያችን በአሳት እየተቀጣጠለ መጣ ሰንጥቅ አጅግ በጣም ጠንካራ ጦር ነው እስካሁን ከሠራሁባቸው ክፍሎች እንደ ሰንጥቅ ያለ ጠንካራ ጦር አጋጥሞኝ አያውቅም የሰንጥቅ ጦርን ከራሴ አመራር ጋር አቀናጅቼ ሳየው ካለ ትዕዛዝ የሚንቀሳቀስ ጦር አልነበረም በተለይም በእኔ ላይ ከፍተኛ እምነት ስለነበረው ትፅዛዜን ያከብራል እልከኛ ጦርም ነው በአንዳንድ ሁኔታዎች ሲታይም አስቸጋሪ ጦር መሆኑን አውቃለሁ አሁን ፍልሚያውን ተያያዝነው «ጥይት እየቆጠባችሁና በጠላት ላይ እያለማችሁ ብቻ ተኩሱ ጠላትን በዚህ ሁኔታ ብቻ ለመቀነስ ሞክሩ። » የሚል ትዕዛዝ ሰጠሁ ከዚህ ውጭ ሌላ አማራጭ ሊኖረን አይችልም ጠላትን ማመናመን የምንችለው በዚህ ስልት ብቻ ነው የሚደንቀው ነገር ቢኖር በስተቀኝ በኩል ካለው መሬት ንጋት ላይ አንድ የመቶ የወገን ጦር ተደመሰሰ የጠላት ጦር በቦታው ላይ እንኳን ሊቆም አልቻለም ቦታ ይዞ በስልት አንደመዋጋት ፋንታ ባገኘው አነስተኛ ድል ተሳክሮ ቁልቁለቱን ወረደልን ወደ እኛ በመውረድ ላይ ያለውን ጠላት በሰፈሩት ቁና እንደሚባለው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዩመሰስነው ካለው ተጠባባቂ የሻምበል ጦር አንድ የመቶ ጦር ልከን ቦታውን ያዝን ተጠባባቂ የመቶው ቦታ እንደያዘ በከፍተኛ ኃይል ጠላት መልሶ ማጥቃት አድርጎ ያንን ቦታ ተቆጣጥሮ በተመሳሳይ ሁኔታ ቁልቁል ወደ ታንኮቹ ወርዶ ታንኮቹ ላይ አስከ መውጣት ደረሰ ሆኖም የተኩስ ሽፋን በመስጠት ከላይ ከነበሩት ታንኮች ጠላት በወጣባቸው ታንኮች ላይ መትረየስ በመተኮስ እንደ ቅጠል አረገፋቸው የሚገርመው ነገር ቢኖር ሌላው እየሞተ አዲሱ ደግሞ እየዘለለ ከእሳት ውስጥ ይማገዳል ጥበቡም ሆነ ወታደራዊ ዕውቀቱ ጨርሶ አይታይም ሁኔታው በእንዲህ እያለ የበላይ አካል ተጠባባቂ ጦር እንዲልክልኝ ባሳስብም አንተ ለቀህ ውጣ የሚል ትዕዛዝ ደረሰኝ በዚህ ዓይነት ሁኔታ መሬት መልቀቅ የባሰ አደጋ የሚጋብዝ ስለሆነ የማይችሉ ከሆነ እንዲተው ለጀኔራል ነጋሽ አንዲሁም ለደኔራል ረጋሳ አሳሰብኩ በተመሳሳይ ሁኔታ ማይኩሊ ላይ የነበረው ሜካናይዝድ ሻለቃ በአነስተኛ የማስመሰል ውጊያ ላይ ቢገኝም ሁኔታውን ገምግሜ አንድ ሜካናይዝድ ሻምበል በአስቸኳይ ከማይኩሊ እንዲላክልሻ ለሻለቃ አዛ ትዕዛዝ አስተላለፍኩ በዚሁ መሠረት ሜካናይዝድ ሻምበሉን ከነብረት ለበሱ አቧራ እያስነሳ እኛ ወዳለንበት ሲመጣ ጠላት ከፍተኛ ኃይል አንደመጣበት በመቁጠር ከማጥቃት ራሱን አላቆ ቁስለኛውን ወደ ኋላ ማሰባሰብና ማፈግፈግ ጀመረ በዚህ ሁኔታ የሜካናይዝድ ሻምበሉ በስተግራ በኩል በመግባት ብረትለበሱ የተኩስ ሽፋን አድርጎ ማጥቃት ሲጀምር በስተግራ በኩል ያለው ጠላት ሙሉ በሙሉ ወደ ኋላ አፈገፈገ ይህንን ሁኔታ በመጠቀም በግራ በኩልና ከፊት ለፊትም ያለውን ጦር ወደ ኋላ ካለው አመቺ መሬት ላይ አንድ አግር በመሬት አያደረጉ እንዲመጡ ትዕዛዝ ሰጠኋቸው ለጊዜው ታንኮቹ የአግረኛውን ሙሉ በሙሉ መውጣት እንዳረጋገጡ ወደ እኔ እንዲቀላቀሉ ትፅዛዝ ደረሳቸው ሆኖም በስተደቡብ በኩል የነበረው አንደኛው ታንክ ባትሪው በመሞቱ ምክንያት መነቃነቅ እንዳልቻለ ታንክ አዛዝዩ እንደነገረኝ ለቀው እንዲወጡ ሳዝ ታንኩን በታንካችን እንደምንደመስሰው እሳቤ በማድረግ ነበር በዚህ ሁፄታ ሁለቱ ታንኮች ወደ አኛ ሲመጡ የፊተኛው ታንክ አንድ ረባዳማ መሬት ውስጥ ገብቶ በመቀርቀሩና ለተኛው ታንክ ማለፊያ በማጣቱ መውጣት አልቻለም ሁኔታው ይህ መሆኑን እንደተረዳሁ ከኛ ብርጌድ ሻለቃ ጦር ከሺራሮ ለእርዳታ ሳናስበው ደረሰልን ሻለቃውንም ከእኔ በስተቀኝ በኩል መልሶ እንዲያጠቃ ሁኔታዎች ሊለዋወጡ ስለሚችሉ ቀሪዎቹን ሁለት ታንኮች በጠላት አጅ ከሚወድቁ እኛው በራሳችን መሣሪያ አጠፋናቸው በዚህ ውጊያ ላይ የኛ አነስተኛ ኃይል አምስት እጅ የሚበልጠውን የጠላት ኃይል በማያውቀው ቦታ ላይ ገጥሞ ከፍተኛ ኪሣራ ማድረሱ የሰንጥቅ ብርጌድን ቆራጥነት ዲሲኘሊንና ጥንካሬን ያሳየ ነው በዚያ ፍልሚያ ወቅት ከማልረሳቸው ገጠመኞች አንዳንዶቹ ትውስታቸው ምንጊዜም ከአዕምሮዬ አይጠፋም ከነዚህም ውስጥ አንድ ሾፌር ልጅ መድፈኛ ውስጥ ነበር በቅርቡም እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ አግኝቼዋለሁ ስሙን ለጊዜው ዘነጋሁት ወታደር ታደሰ ይመስለኛል ጓደኛው በጦርነቱ ላይ ተመትቶ ተሰውቷል በዚህ የጥይት ዶፍ ውስጥ ያንን የጓደኛውን አስከሬን አንስቶ ወደ አንድ ተዳፋት ውስጥ ወስዶ ጉድጓድ ይቀፍራል «እንዴ። » ስል ጠየቅኋቸው «ልጄ ምንም ነገር የለኝም» አሉ ከያዝነው ቀለባችን ስኳር ወተት የቲማቲም ድልህ ማርማላታ የመሳሰሉትን በአንድ ጆንያ ውስጥ ቋጥረን ሰጠናቸው ከዚያ በኋላ የመንገዱን አቅጣጫ ጠየቅንና የአካባቢው ሽማግሌዎች ነገሩን መንገዱ ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ስለነበረና ፈንጂም ይኖረዋል ብለን ስላልጠረጠርን ጉዞ ቀጠልን ገዞዋችንን እንደቀጠልን ከሁለት ቀን በፊት ከእኛ ጋር ሲዋጉ ከነበሩት የተረፉት ቁስለኞቻቸውን ይዘው ወደ ሳህል በረፃ ለመውሰድ በዚያ መንገድ አቋርጠው አልፈው ኖሯል በመንገዱ ላይ ፋሻ የጉልኮስ ላስቲክና የመሳሰሉት ባለፉበት አቅጣጫ ላይ ተንጠባጥበው ወድቀዋል የፈሰሰ ደም ሁሉ በየሣሩ ላይ ይታያል «ቁስለኞች በመንገድ ላይ አልፈዋል ለማለፋቸውም የተለያዩ ምልክቶች ታይተዋል እስቲ ወደፊት ገፍቼ ልሞክር» አልኩና ለሜጄረጋሣ ጂማ መልዕክት አስተላለፍኩ ከግዳጃችሁ አቅጣጫ ውጭ ወደ ሌላ መሄድ አትችሉም» የሚል መልስ ሰጡኝ የሚገርመው ነገር ከዚያ በኋላ የጠላት ወታደር የነበሩትን አግኝቼ ሳነጋግራቸው በዚያን ወቅት ሁሉም ቁስለኞች በጣም ተስፋ ቆርጠው እንደነበር አጫውተውኛል በዚያ ወቅት የእኛ ታንክ በአካባቢው ሲያልፍ አቧራውንም ያያሉ ድምፁንም ይሰማሉ በወቅቱ ብናገኛቸው ምን ማድረግ አንደሚቻል በጣም ያስቸግር ነበር ቁስለኛን መግደል ደግሞ በዓለምአቀፍ ሕግ የተከለከለ ስለሆነ ለቀጣዩ ሥራችን እንቅፋት ይፈጥርብን ነበር ያለን አማራጭ በምርኮኛ መልክ መውሰድ ብቻ ነበር ከዚህ በኋላ ጉዞአችንን ወደ ተከዜ ቀጠልን አንዳንድ የጠላት ቃሺዎች ትንሽ ተኮሰብን መታመታ አደረግናቸውና ተከዜ ደረስን ተከዜን ተሻግረን አፋፍ ላይ ወጣን ከሁመራ የሚንቀሳቀስ ሚሊሺያ ብርጌድ ነበር ሕዝባዊ ሠራዊት ጭምር የታከለበት ነው በኮሎኔል ተመስገን በኋላ ጀኔራል የሚመራ ጦር ነው ጦሩ ትንሽ የተዝረከረከ ቢሆንም ከዚህ ጦር ጋር ተቀላቅለን ጠላትን መጠባበቅ ጀመርን የጠላት ጦር ግን ወደ አኛ አልመጣም ከእኛ በስተቀኝ በኩል አልፎ አዲጎሹ ገደማ ነበር የሄፄደው እኛም ተመለሱ ተባልን በኮሉኔል ተመስገን የሚመራውም የሚሊሽያ ጦር ወደ ሁመራ ይሂድ ተባለ እኔ ገን የዚህ ጦር ሁኔታ በወቅቱ ደስ አላለኝም ማታ ማታ መብራት ያበራል የጥበቃ ሥርዓቱ ሁሉ የላላ ነው ኡፌ ፌፌፎ ይህንን ጦር አዲጎሹን አሳልፌው ልመለስ» የሚል ጥያቄ አቀረብኩ ጀኔራል ረጋሣ ጂማ ደግሞ «እኛ ተመለሱ የሚል ትዕዛዝ ነው የተሰጠን የበላይ ትዕዛዝን መጣስ አንችልም አሉ ይፄ ጦር እኮ ብቃት የለውም እኛ ደግሞ በቂ መሣሪያ አለን ጠላት በአሁኑ ጊዜ በሽሽት ላይ ቢሆንም ሰው ሲመለስ አይቶ ደፈጣ ሊያደርግ ይችላል የሚል ግምት አለኝ አልኳቸው ሊቀበሉኝ ግን አልቻሉም እኔ በገመትኩት መሠረት ይህ ሚሊሽያ ጦር ወደ አዲጎሹ ሲመለስ የጠላት ጦር ደፈጣ አድርጎ በአደረበት ቦታ ላይ ጉዳት አደረሰበት ያን ያህል የተለፋበት ዘመቻ ይህንን የመሰለ ጉዳት ሲደርስበት በጣም ያሳዝን ነበር ይህንን እኛ የሰማነው ማይባሬ ደርሰን ወደ እንጥብጣብና ሲቶና አቅጣጫ ሂዱ በተባልንበት ወቅት ነው አውሮኘላኖች ጉዳት በደረሰበት አካባቢ ደርሰው አንዳንድ የተረፉ መኪናዎችን አቃጥለዋል የእኛ ጦርም ተመልሶ ድጋፍ ሊሰጥ የሚችልበት ሁኔታ አልነበረም በቀይ ኮከብ ዘመቻ የሻዕቢያን ጦር ያጠናከረ የህወሐት ጦር ስለነበረ በ ዓም ኤርትራ ውስጥ ሌላ የዘመቻ ዙር ታቀደ የዘመቻው ዓላማ በቅድሚያ ህወሐትን አዳክሞ በሻዕቢያ ላይ ሌላ ዘመቻ ለማካሄድ ነውጉዞዋችንን ወደ ሸላሎ አደረግን ሕዝቡ መስቀሉንም ታቦቱንም ይዞ ተቀበለን ገና ከሩቅ ሲያየን ሕዝቡ ሁኔታው ሰላም መሆኑን ሲገልጽልን አኛም ሰላማዊ መሆናችንን ነገርናቸወ አንዳንድ ጥያቄዎችን ጠየቅናቸው አዳር አደረግንና በማግሥቱ ከዚያ ተነስተን ባሬንቱ ገባን በሚቀጥለው ቀን ደግሞ አቆርዳት ደረሰን አቆርዳት እንደገባን ቀድሞ ከእኔ ጋር የነበረው ኛ እግረኛ ብርጌድ ጠንካራ ስለነበረ እንደገና ደግሞ ሰንጥቅን ማጠናከር አስፈላጊ ስለሆነ ከሰንጥቅ ጋር ተዋህዶ ጠንካራ ብርጌድ እንዲሆን ር ዬዴ ስለታመነበት ኛ ብርጌድ ከሰንጥቅ ጋር እንዲዋሀድ ትዕዛዝ ደረሰኝ ኛ ሰንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ ተብሎ እንዲሰየም ተደረገ ጠንካራ ተዋጊና ጎበዝ የሚባሉ መኮንኖች የበታች ሹሞችና ወታደሮች ተመረጡ የመጀመሪያው ሻለቃ ኛ የተባለው የኛ ብርጌድ ሰዎች ብቻ ነበሩ ኛ ሻለቃ የኛ ብርጌድ ቀደም ሲል በቀይ ኮከብ ዘመቻ የተቋቋመ ኛ ሻለቃ ደግሞ የኛ ሻለቃ ሆነው ተቋቋሙ ለውድድርም ለእርስ በርስ መግባባትም አመቺ ነው የዱሮ ክፍላቸውንና ታሪካቸውን እንዲጠብቁ ተነገራቸው ከዚያ የተራረፉት ወደ ብርጌድ ጠቅላይ ሠፈር አልፎ አልፎም ኃይል ወደጎደለባቸው ሻለቆች ወስጥ እንዲሟሉ ተደረገ በመሠረቱ አንድ ጓድ በሜካናይዝድ ብርጌድ ውስጥ ሰው መሆን አለበት ነገር ግን እኔ እንዲሆኑ አደረግሁ በውጊያ ላይ የሰው ኃይል ቢቀንስ ተተኪ ኃይል አለኝ ማለት ይቻላል ይህ የእኔ አመራር ነበር ያ ደግሞ ባውጊያ ላይ በጣም ጠቅሞኛል ከዚያ በኋላ የ ቀን የጦር ልምምድ አደረግን የቆሰሉትም በምግብ ሰውነታቸው የሚመለስበት መንገድ ተመቻቸ በሰንጥቅ ጦር ውስጥ በጣም የሚደነቀው ነገር ቢኖር በውጊያ ላይ የቆሰለ ወታደር አዲስ ውጊያ ሲከፈት ገና ፋሻው ሳይፈታ ነበር ከጓደኞቼ አልለይም ብሎ ሮጦ ጦር ግንባር የሚሰለፈው ከልምምድ በኋላ ሜጀር ጀኔራል ኃይለጊዮርጊስ ኃብተማርያም በቦታው ተገኝተው ሚስጥርነቱ እንዲጠበቅ የተፈለገ የቃል ትዕዛዝ ሰጡኝ «በነገው ዕለት ተነስተህ አሌት አንድትገባ። አሉኝ አሺ አልኳቸው «ለማንኛውም ትዕዛዙ በሚስጥር አንዲጠበቅ የሚል መመሪያ ሰጤጡኝ ዘመቻ ከርከበት ኛ ክፍለ ጦር በአግሩና ባለው መኪና እየመጣ ነው ባሬንቱ ገብቷል ወደ አሌት ለመሄድ መንገዱን ብንከተል ፈንጂ እንደሚጠቀጠቅበት ስለማውቅ በተኸረሪት ግራውን አድርገን ጫካ ጫካውን ሰባብረን ደረቋን ወንዝ ተሻግረን ምንም ፈንጂ ሳያጋጥመን አሌት ገባን ቦታው ላይ መድረሳችንን ለበላይ የሬዲዮ መልዕክት አስተላለፍኩ በጣም ደስ አላቸው የሚያስደንቀው ነገር የበላይ ለእኛ ሚስጥር ብሌ ያስተላለፈውን ትዕዛዝ ተግባራዊ ሳናደርግ በፊት ቀደም ሲል ደደቢት ላይ ሲዋጋን የነበረው የጠላት ጦር ኃይሉን አሟልቶ ሚስጥሩ ደርሶት ሻዕቢያን ለማጠናከር ካለበት ተልኮ አሌት ሊገባ ኪሜትር ገደማ ሲቀረው በውፃ ጥም ተሰቃይቶ ወድቋል ይህንን የነገሩን በሚቀጥለው ቀን ሳታ ስንደርስ ከእነሱ የከዱ ሁለት ልጆች ናቸው እኛ ዓን ተልአኳችንም ምስጢራዊ ስለሆነ ይሄ ሁኔታ ይፈጠራል ብለን አልገመትንም ጠላት መልሶ ተቋቁሞ ይንቀሳቀሳል የሚል ግምትም አልነበረንም እኔ ደግሞ አሌት ሜዳ ስለሆነ ምንም ነገር አይኖርም የሚል ግምት ስለነበረኝ እንጂ ጠለቅ ብለን ብንቃኝ ልናገኛቸው እንችል ነበር የጠላት ጦርም የሰንጥቅን መምጣት ሲሰማ ተስፋ ቆረጠ ከበላይ አካል ግን አልፈህ ሳታ ሂድ የሚል ትዕዛዝ ተሰጠኝ ወደ ሳታ ሄድን ሳታን ይዘን ሁለት ሶስት ቀናት ገደማ ቆቁየን የህወሐት ብርጌድ ኩር ውስጥ ገብቶ በቀይ ኮከብ የተዘጋጀውን ምሽግ ያበዘ ይህ ምሽግ የኛ ጦር በከርከበት ግንባር ሊይዝ ያልቻለውና የተመታበት ምሽግ ነው አራት ቀን እንደቆየን ኛ ሜካናይዝድ ብርጌድ ከአቆርዳት ተነስቶ መጥቷልና ሳታን ለዚህ ብርጌድ አስረክበህ ወደ ኩርከርከበት አንድትገባ የሚል ትዕዛዝ ደረሰኝ ብርጌዱን ብጠብቅ ፈጽሞ ሊመጣ ብ መው መመመ አልቻለም ለካ ይሄ ጦር በድሮው መንገድ ፄዶ ከፈንጂ ውስጥ ገብቶ ኖራል በርካታ ፈንጂዎች መቱት «አናንተ የሄፄዳችሁበትን አቅጣጫ አመልክቱት» የሚል መልዕክት ደረሰኝ ሁለት ብረትለበስ ቃፒዎች እንዲሄዱ አደረግሁ ከቃፒዎቹ ጋር ተገናኘና አቅጣጫውን ተከትሎ ደረሰ ሳታን ለዚህ ጦር አስረከብኩና እኛ እንደገና ወደ ከርከበት ተመለስን ከዚያ አንድ አግር በመሬት በማድረግ ጥንቃቄ በታከለበት ሁኔታ ቅኝት እያደረግን ጠቃሚ መሬቶችን በመያዝ ኩር ላይ ደረስን እዚያ እንደደረስን ከጠላት ጋር ተያየን የጠላት ቃዎች የያዙትም ጊዜያዊ ምሽግ ነው ዋነኛው ግን በደንብ በተቆፈረው በቀይ ኮከብ ምሽግ ውስጥ ነበሩ በቅድሚያ ያገኘናቸውን እየመታን መሣሪያችንን እያስጠጋን ቀረብናቸው እንጂ ዘለን አልገባንም የውሃ ነጥቧን ኩርን ያዝን ከግራም ከቀኝም የወገን ጦር አልነበረም ከኛ ክፍለ ጦር ኛ አግረኛ ብርጌድና ኛ ሚሊሽያ ብርጌድ ደረሱልንና ከእኛ በስተቀኝ ገቡ አንደገና ኛ ክፍለ ጦር የሚባል ደግሞ ከዐ ቀናት በኋላ ቆይቶ መጣና በስተግራ በኩል ገባ ኛ ብርጌድ በሳታ በኩል የሻዕቢያ ኛ ብርጌድ እኔ ባለሁበት ግራ የህወሐት ኛ ብርጌድ ከእኔ ፊት ለፊት በስተቀኝ በኩል ሻዕቢያ ዐኛ ብርጌድ ከኛ ክፍለ ጦር ፊት ለፊት የመከላከያ ቦታ ይዘዋል ከኛ ክፍለ ጦር ጋር እየተመካከርን የቀይ ኮከብ ምሽግ አስከሚታየን ድረስ ቀረብን በተለይ በአኛ በኩል ግልጽ ሆኖ ይታያል በዚያን ወቅት ኛ ብርጌድ ስጋት ላይ ወድቆ ነበር ያ ባለሰንሰለታም ጦር ፓ ጣብን አያሉ ይናገራሉ ወዶገቦች አንደነገሩን ቀደም ብሉ ጡንቻችንን ቀምሏሷል በዚያን ጊዜ አንዲት ስላላገኘ መንገድ ከ። በሚል እያሰላሰልኩ ተነስተን ሄድን ኛንና ሳታን ወደ ቀኝ ትተን ከሜዳው ወጣን ከአሸዋውና ከከዋክብት ብርዛን ጋር ተቀላቅሎ የእይታ ችግር አልነበረም ያን ሁሉ መሣሪያና ታንክ ማንጋጋት በንብረት ላይ መጫወት ነበርጹ እንደ ፊርም ቤዝ የመታኮሻ ቦታ ዓይነት ያዝን ጥቂት ቢአርዲኤሞችና ቢቲ አሮችን በቀጣዩ በየአቅጣጫው እንዲላኩ አደረግሁ ነገር ግን በዚያ አካባቢ እንኳን ጠላት ወፍ አልነበረም አስከ ጠረፍ ድረስ ተጓዝን በአካባቢው ጦር እንዳለፈ ሕዝቡን ጠየቅንና ምንም ነገር እንደልነበረ ተረዳን በከ ን በዚህ ሁኔታ ቅኝቱን እንዳበቃን እዚያው አዳር አደረግን ሁኔታውን ለቅርብ አዛቱቼ ሪፖርት አደረኩ ጠላት ካለበት አካባቢ የራቅን ስለሆነ ቢያንስ አሌት እንድንመለስ ጠየቅሁ የሚቀጥለውንም ቀን ጥቂት ቃኘንና ወደ አሌት ተመለስን ከአሌት በማለዳ ሰኔ ዓም ተነስተን ከርከበት ለመግባት ጉዞ እንደጀመርን ኩር ላይ ጦርነት ስለተከፈተ ቶሎ እንድትደርስ የሚል ጥሪ ከግብረኃይሉ ደረሰኝ ከዚያ ወደ ኩር ስመለስ በስንት መስዋዕትነት የያዝነው ጋራ ተለቋል ይዘነው የነበረው ቦታ ሁሉ በሙሉ በጠላት ኃይል ተይዛል መልሶ ማጥቃት ለማድረግ ሰንጥቅም ኛና ኛ ክፍለ ጦሮችም ሞከርን ግን አልተቻለም ከዝቅተኛ ቦታ ወደ ከፍተኛ ቦታ ማጥቃት ቀላል አይደለም ያን እለት እኔም ሆንኩ ሠራዊቱ የተበሳጨነውን ብስጭት ይፄ ነው ብሎ ለመግለጽ ያስቸግራል ለጊዜው እዚያው ኩር ላይ ውዛ ነጥቡን ወደራሳችን አድርገን ያዝን ኛ ክፍለ ጦርን ከእኛ ው ጋር አስተካከልን ጠላት ከኋላ ገብቶ ለማጥቃት ሙከራ አደረገ ትንሽ መታ መታ አደረግነውና ወደ ኛ ክፍለ ጦር አቅጣጫ ተጓዝን የጠላት ጦር አላማ ግን አሱን ገፍትሮ ያስቸገረው እዚህ አስማጥ ውስጥ ያለው ጦር ስለነበረ አሱን መልሶ አጠቃ ኛ ክፍለጦር ደግሞ ወደ ኋላ ወደ ዐ ኪሎ ማትር ረባዳማ ቦታ ላይ ነበር ግብግቡ ቀላል አልነበረም በጐን ጠላት ኛ ክጦርን በመገፍተር ብዙ አልፎ ነበር ከዚያ በኮሎኔል ሠረቀብርፃን የሚመራው ዐኛ ብርጌድ እንደምንም ብሎ አንድ ከፍተኛ መሬትን ይዞ ተአከላከለ ከዚያ በኋላ ኛም ከዚያ ረባዳማ ቦታ ወጥቶ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎ የመለብሶ ከፍተኛ መሬቶችን መያዝ ተቻለ በዚህን ጊዜ የኛ ክፍለ ጦር አካል ኛና ኛ ብርጌድ በአስቸኳይ ወደ አቆርዳት እንዲመጡ ኛ ክፍለ ጦርም እንዲመጣ ሳታ ያለውም ኛ ወደ መለብሶ እንዲገባ ተባሰለ ልክ እንደ ቀይ ኮከቡ ዘመቻ ጊዜ አሁንም እኔ ወደ ኋላ እንድቀር ተደረገ እኔም ብቻዬን ቀረሁ የጠላትም ሀሳብ ወደዚያ መገስገስ ነበር እኔ የምመራው ጦር ግን በርካታ መሣሪያዎች ነበሩት አንድ ሻምበል አጃቢ አድርጌ ያለ የሌለውን የጦሩን ንብረት በሙሉ ወደ አቆርዳት እንዲጓጓዝ አደረግሁ የሚያሳዝነው ግን በዚያ የውጊያ ሂደት ውስጥ ከከርከበት ወንዝ በላይ ማዘዣ ጣቢያቸውን ያደረጉት የመጀመሪያ ግብረኃይል አዛዥ ቤት ያሠሩ ነበር ይሄ የሚሠሩት ቤት ምንድነው። » ስለው «የወገን ጦር ነው» የሚል መልስ ይሰጠኛል ነገር ግን የወገን ሳይሆን የጠላት ጦር ነበር ቀረብ ብሎ ያለ ማየት ጉዳይ ነው ከዚያ የኛ ተራራ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል በኋላ ጀኔራል አሸቱ ያሉበትን ጠይቄ አንድ ሻለቃ ጦር በመያዝ ለማጠናከር ወደዚያ ሄድኩ ጠላት ቦታ እያስለቀቀ በመሆኑ ጦሩ አፈገፈገ እሳቸውም እንድመለስና ፄርሜትን ቀድሜ እንድይዝ ትዕዛዝ ሰጡኝ ስንመለስ የግራ ክንፋችንን በሙሉ ጠላት ተቆጣጥሮታል ሳናስበው ከፊትም ከኋላም ተኩስ ተከፈተብን ከዚህ ረባዳማ መሬት መውጣቱ አስቸጋሪ ነውፊ ኛው ሻለቃዬ ደግሞ በመርገመት ግንባር በኩል አንደዚሁ ውጊያ ስለተከፈተበት የቀረኝ አንድ ሻለቃ ብቻ ነው በጦር ሜዳ መነጽር ስመለከት በስተግራ ክንፍ ያለው ወደ ሔርሜት መተለለፊያ እየገሠገሠ ነው ስለዚህ ኛ ሻለቃን በአስቸኪይ ቢችሉ በመኪና አለዚያም በአግር የሔርሜት መተላለፊያን እንዲይዝ ትዕዛዝ አስተላለፍኩ ከእዚያ ውጊያው ተጧጧፈ እንደምንም ብለን እንዳንከበብና አንዳንቆረጥ የግዴታ ከዚያ ቦታ መውጣት ነበረብን በወቅቱ ኮሎኔል እሸቱ በስተግራ ፌዴ ን በኩል ያለውን የሔርሜት መተለለፊያ እንዲይዙ እኔ ደግሞ ከመንገዱ በስተቀኘ ያለውን ለመያዝ ኛ ሻለቃ በአስቸኳይ እንዲገባ ቀደም ብዬ ትዕዛዝ ስለሰጠሁ በዚሁ ተስማማን ያ ሻለቃ እዚያ ቦታ ላይ ቀድሞ ባይደርስ ኖሮ ውስጥ በቀረን ነበር ለማንኛውም በረባዳማ መሬቱ ውስጥ እየተሽሎከሎክን የሔርሜት መተላለፊያን ያዝን ጠላትም ወጣ ከሔርሜት መተላለፊያ በቀኘ በኩል አንድ ከፍተኛ መሬት አለ ይሄ ከፍተኛ መሬት በወገን ጦር አልተያዘም ከኛ ሻለቃ ወስጥ ሻምበል በአስቸኳይ ያንን ከፍተኛ መሬት እንዲይዝና ሸጡን እንዲዘጋ አዘዝኩጃ የሻለቃው አዛዥ ያኔ ሻምበል ገብረሚካኤል ኩምሲሳ ይባላሉ አሁን ጠላት ወደፊት እንዳይገፋ አደረግን በስተግራ በኩል ግን ያለው ውጊያውን ቀጥሏል ሁሉም ነገር በዚህ ዓይነት መልኩ ተስተካከለ በመርገመት ማዘዣ ጣቢያ ያለበትም ቦታ ተለቀቀ ጀኔራል ውበቱም ወደ ድሮው የቀይ ኮከብ ምሽግ ተመለሱ። » የሚል መልዕክት ለአለቃዬ አስተላለፍኩ የሚሆን ነገር አልነበረም ወደ ቀይ ኮከብ ምሽግ ተጠናቀን እንድንገባ ስለታዘዝን ወደዚያው ገባን የቀይ ኮከብ ምሽግ ኛ ክፍለ ጦር የሠራው ጥሩ ምሽግ ነው ጠላት እኛ ንም አልተከተለም ወደፊትም መግፋት አልፈለገም እዚያው ሁለት ቀናት ገደማ ከቆየን በኋላ ወደ አፍአበት ፄደን ተጠባባቂ አንድንሆን ተደረገ የ ዓም ዘመቻ እጅግ በጣም አስደናቂ ውጤት የምናገኝበት ነበር ይሁን እንጂ አላስፈላጊ የጦር መለወጥና የምስጢር መባከን ስለነበረበት ድልን ሊያስጨብጠን የነበረው ዘመቻ በተፈጠረው አሻጥር ከማጥቃት ወደ መከላከል ገባን ቀደም ብሎ በተዘጋጀው የቀይ ኮከብ ምሽግ ኛ ተራራ ክፍለ ጦር እና ኛ ተራራ ክፍሉጦር ነበሩ በዚያ አካባቢ መርገመትና ሔርሜት ላይ የነበሩት እነሱ ስለነበሩ በዚያ ምሽግ ውስጥ ገቢ ይሁን እንጂ የእኛ የሥራ ባህርይ ሜካናይዝድ ስለነበር አዙ ደግሞ ጠንካራ መቺና ተጠባባቂ ሪዘርቭ ኃይል የሌለው በመሆኑ በመንግሥት ትዕዛዝ እኛ ወያ አፍአበት እንድንገባ ተደረገ ያ ትፅዛዝ ከመሰጠቱ ከአንድና ከሁለት ቀናት በፊት ኘሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ቦታው ድረስ መጡ ር ፒን የደረሰውም ሁኔታ በጣም ስላሳሰባቸው አዛችን እኔንም ጭምር ለማነጋገር ፍላጎት ቢኖራቸውም ያለንበት ሁኔታ ስላልፈቀደ አደራውና መልዕክቱ ብቻ ተላለፈልን ከአንድ ሁለት ቀናት በኋላ ከመከላከል ግንባር ወጥተን አፍአበት ላይ ተሰባሰብን ዋናው ግዳጃችን የእዙ ተወርዋሪ ኃይል መሆን ነው ተወርዋሪ ኃይል ማለት ደግሞ ብቃት ያለው የመነቃነቅ ችሎታው መቶ በመቶ የሆነ ድንገት ጠላት ቢያጠቃ መልሶ ማጥቃት የሚችል ነው እኛ ደግሞ ሜካናይዝድ ጦር ስለሆን ፃይል ብቻ ሳይሆን በቂ መሣሪያም ነበረ ኛ ሠንጥቅ በሜካናይዝድነቱና በተወርዋሪነቱ በኤርትራ ምድር ውስጥ አንቱ የተባለ ጦር ነው ይፄ እኔ የምመሰክረው ሳይሆን ጠላትም የመሰከረውና ሁሉም ቢሆን የሚያውቀው ነው አንዳውም ትዝ ይለኛል በአንድ ወቅት ሻዕቢያ አንድ ሻምበል የማይሞላ ጥቂት ታንኮች መድፍና አየር መቃወሚያ የመሳሰሉት የሚገኙበት አንድ ሻለቃ ጦር ፈጥሮ ለዚያ ጦር የሰጠው ስም ሰንጥቅ ነበር ይህንን ያደረገው ያለ ምክንያት አልነበረም እኔም የዚህ ዓይነት ጦር አለኝ ለማለት ነው በዚህ መሠረት እኛ በቅድሚያ ጠላት ሊያጠቃቸው ይችላሉ የሚባሉትን መስመሮች ማለትም ከሔርሜት ፊት ለፊት ወይም ከቀለማት ወንዝ አንስቶ አስከ ገምገም ያለውንና ብዙ ኪሎ ሜትር ሊሸፍን የሚችለውን ሰፊ መሬት ያካተተ ግዳጅ ነው የተሰጠን በዚህ ግንባር ላይ ጠላት ሊያጠቃ ይችላል ጠላት በዚህ መስመር ላይ ቢያጠቃ እኛ አንዴት መልሰን ማጥቃት እንችላለን። ኡሙጦ ዚሠ ዘመቻ አረዛና ወደ አፋአበት መልስ በ ዓም በድንገት ጠላት አረዛን አጥቅቶ ወደ መንደፈራ ይገፋል የሚል ስጋት ስለነበረ ሰንጥቅ ከአፋአበት ተነስቶ በጀርባው አቆርዳትባሬንቱከባሬንቱቦሾቃ ከቦሾቃ ወደ ሙልቂ እንድንገባ ትፅዛዝ ተሰጠን ይሄ አቅጣጫ ወይም መንገድ ከዚህ ቀደም ከንጉሥ ጊዜ ወዲህ በደርግ ጊዜ ማንም ሰው ያልተነቃነቀበት መንገድ ነው ስለዚህ ጠላትም በዚያ በኩል ይመጣሉ የሚል ግምት አልነበረውም በተለይ ሜካናይዝድ ለሆነ ኃይል በጣም መጥፎ አቅጣጫ ነው ከአፉአበት በጥዋት ተነስተን አቆርዳት ገባን አቆርዳት ቀሪ ክፍላችንም ስላለ የሚያስፈልጉ ንብረቶችን እዚያ ትተን ለዘመቻ ብቻ ይሆነናል የምንለውን ይዘን በማግስቱ ገባን ባሬንቱ እንደገባን የዘመቻው ትዕዛዝ በዕዙ አዛዥ በጀኔራል መርዕድ ንጉሴ በፅሁፍም በካርታም ተደግፎ ተሰጠን እኔ እንኳን በ ዓም ወደ ትግራይ ስለፄድን በተኮምቢያ አቅጣጫ ወደ ሲቶና የሚወስደን ነበር የመስሰለኝ ከካርታውም ላይ ስመለከት ከቦሾቃ በቀጥታ ወደ ሙልቂ ከሙልቂ ወደ አረዛ ከአረዛ ወደ መንደፈራ የሚወስድ ነበር ይህ ትዕዛዝ ሲደርሰኝ በጣም ግራ ተጋባሁ በመጀመሪያ በዚያ አቅጣጫ ሰው ተነቃንቆ አያውቅም ሁለተኛ ምንም እንኳን በካርታው ላይ የመንገድ ምልክት ቢኖርም በርካታ ማነቆ ቦታዎች አሉ ከሙልቂ ወደ ምዕራቡ ካለሰው ሜዳማ ቦታ ላይ ከተወጣ ምንም ችግር የለውም እስከዚያ ድረስ ግን ጠመዝማዛና ወንዞች ያለበት ቦታ ነው ድንጋያማ መሬት ስለሆነ ለብረትለበሶች በጣም አስቸጋሪ ነው ስለዚህ ሁኔታው ትንሽ አላሳሰበን ይሁን እንጂ ለሚመለከታቸው አዛፐች ትዕዛዝ ሰጠሁ ነገር ቢኖር በእጁ ይዞት የነበረውን የሬዲዮ ኮድ ከመሞቱ በፊት አፉ ውስጥ አስገብቶ በጫጭቆ ግማሹን ውጦት ቀሪውን ደግሞ አላምጦት ምላሱ ላይ ማግኘታችን ነው ከአድናቆቴ በተጨማሪ በጣም ተናድጃለሁ ምክንያቱም በሕይወት ብናገኘው ኖሮ ብዙ መረጃ ማግኘት ባስቻለን ነበር ነገር ግን ምስጢሩን አሳልፎ ሳይሰጥ መስዋዕት መሆኑ አስደንቆኛል ምንም እንኳን ጠላት ቢሆንም አስከሬኑ በስርዓት እንዲቀበር አድርገናል ይህ ደግሞ ለእኛም ወገን ቢሆን ሞራል የሚሰጥና የአንድን ጠንካራ ወታደር ዲስኘሊን ምንነት የሚያስተምር ነው ሽ ጠላት ሌሊቱን ጥቃት ይሰነዘርብናል የሚል ግምት ነበረን ጠላት አረዛ ላይ ውጊያ እያደረገ ስለነበረ ከዚያ ተነቃንቆ አኛ ካለንበት ድረስ ለመምጣት አንድና ሁለት ቀን ስለሚፈጅበት ያ ደግሞ ከአቅሙ በላይ ነው አኛ በማግሥቱ ከሌሊቱ ሰዓት ገደማ ተነስተን አስፈላጊዎቹን ቁልፍ መሬቶች እየያዝን ቃፒዎቹንም ወጠደፊት በመላክ መሐንዲሶችም መንገዱን እንዲፈትሹ በማድረግ ግብ ሆኖ ከተሰጠን ሙልቂ ገባን መሙልቂ አነስተኛ መንደር ናት ጫካና ሰበርባራ ሸጦች ያላትለጥበቃ እጅግ አስቸጋሪ ቦታ ናትቡ ሙልቂ እንደደረስን ይዞታችንን አስፍተን በመያዝና ከፍ ባሉ ጉብታዎች ላይ ቃኝዎችን በመላክ ጠላት በላያቸው ላይ መኖርና አለመኖሩን ለማየት አሰሳ አደረግን ሻዕቢያ በደጋው አካባቢ ቁስለኞችን ሳህል ከመውሰዱ በፊት እንዲታከሙና አንዲያገግሙ የሚያደርው በዚህ አካባቢ ነው በመንደሩ አንድ ቦታ ላይ በፓኬት በፓኬት ያሉ አትክልቶችና የአትክልት ዘሮች አሉ የኪነት ልብሶች መድሐኒት የመሳሰሉት ሁሉ አንድ ቦታ ላይ ተከማችተው አገኘ ናቸው መጥፋት የነበረበትን አጠፋን ጠቃሚ የመሰለንን ደግሞ ያዝን በጉዞ ላይ እያለን ውጊያ ካልተከፈተ በስተቀር ማንም ወታደር ከብረት ለበሶችና ከመኪናዎች ላይ አንዳይወርድ ነገር ግን ግራና ቀኝ መሣሪያችንን አዙረን በነቃ ጥበቃ መጓዝ እንዳለብን ትዕዛዝ ሰጠሁ ይሁን እንጂ ወደዚያ አቅጣጫ አንድንጓዝ ከበላይ የተሰጠው ትዕዛዝ በጣም አደገኛ ነጡ ምክንያቱም ጠላት በመረጃ ደርሶ በቅርብ ያለውን ተወርዋሪ ኃይሉን ቢልክ እንቅፋት ስለሚፈጥርብን ውጤቱ አያምርም ለተሰጠን ትዕዛዝ ተፈፃሚነት የተቻለውን ጥንቃቄ አድርገን ጉዞ ጀመርንና መጀመሪያ በሸቃ ደረስን ከዚያ ቦሾቃን አልፈን ወደ ሙልቂ ወደሚወስደው ተረተርና ወንዝ ውስጥ ገባን ቦታው ለብረት ለበስ ንቅናቄ በጣም አስቸጋሪ ነው ከፊት ታንኮች ከኋላ ብረት ለበሶች አድርገን በቀጥታ ቀዳሚው ጦር ሙልቂ አካባቢ ሳይደርስ አንድ ሰፊ የአርሻ መሬት አገኘን ከአንድ ከፍተኛ መሬት ላይ ወጥቼ አካባቢውን ስመለከት ከመንገዱ ግራና ቀኝ በጫካ የተሸፈነ መሬት ታየኝ ያ ሙልቂ ነው እየመሸ ስለሄደ ያንን አልፎ መሄድ አደጋ መጋበዝ መስሎ ሰለታየኝ ከአርሻማ በቦታው ላይ ልዩ ልዩ ክፍሎችን ቦታ አስይዘን ከፍ ከፍ ካሉት ጉብታማ ቦታዎች ላይ ደግሞ የተወሰነ ጦር ለጥበቃ አውጥተን አዳር በዚያ ቦታ አደረግን እንዳጋጣሚ ሌሊቱ ጨረቃማ ስለነበረ የእኛን አዚያ መግባት ያላወቁ ወይም ከረጅም ርቀት የሚጓዙ አንድ የጠላት ካድሬ ኃላፊና አብረውት የነበሩት ሁለት ወታደሮች በአንድ አህያ ላይ የተወሰነ ጥይትና ቀለብ ጭነው አገር ሰላም ነው ብለው ወደ ሙልቂ አቅጣጫ ሲሄዱ የእኛ ቃፒዎች ከመተኮሳቸው በፊት እንዲቆሙ ማስጠንቀቂያ ከሰጧቸው በኋላ አህያዋን ሲነዳ የነበረው የጠላት ወታደር ወደ ኋላ ሲያፈተልክ ሁለቴ ከሚያመልጡኝ ብሎ ተኩሶ ይጥላቸዋል ተመትተውጡ ከወደቁት አንደኛውና ኃላፊ የነበረው ካድሬ ቀደም ሲል የጊትዮጵያ ባህር ኃይል ባልደረባ የነበረ መሆኑን ከዱሮ መታወቂያው ልንረዳ ችለናል በጣም ያደነቅሁት የኛን ሙልቂ መግባት የሰማው ጠላት አንዳይቆረጥ ውጊያ አቁሞ ወደ ሌላ አቅጣጫ አፈገፈን አንድ ሶሰት ቀናት የህል አዚያ በመቆየት በስፋት ቅኝት ብናደርግም የገጠመን የጠላት ኃይል አልነበረም በወቅቱ የክፍለ ሀገሩ የኢሠፓ ዋና ፀሐፊ ዶር ተፈራ ወንዴና የሰሜን ዕዝ አዛዥ ማጀነራል መርዕድ ንጉሚ በአንድነት ቦታው ድረስ መጡ ስላደረግነው ወታደራዊ ተልዕኮ ከፍተኛ ምስጋና አቀረቡልን አኛም ደግሞ ለሌሳ ግዳጅ የምንፈለግ ስለሆነ ሌላ ጦር መጥቶ አንደሜተካንና በማግሥቱም እንደምንወጠጣ መመሪያ ተሰጠን በመመሪያው መሠረት ለአንድ ብርጌድ ጦር ከአንድ ታንክ ሻምበል ጋር አስረክበን ወጣን ሁኔታው ግን በጣም አሳሰበኝ ምክንያቱም ያ ጦር በዚያ ጥልቀትና መጥፎ ቦታ እራሱን እንኳን መከላከል እንደማይችል ነበር የተረዳሁት ለሚመለከተውም የበላይ ኃላፊ በወቅቱ አስረድቻለሁ ብዙ ጊዜ የሚያሳዝነን ነገር ቢኖር ከወታደራዊ ፅውቀት ማነስ ወይም ከሁኔታዎች አስገዳጅነት የተነሳ እያወቅን የምንጠፋና የምንደመሰስ ሰዎች መሆናችን ነበር ሙልቂ አስትራቴጂካዊ የሆነ ቦታ አልነበረም ጠላት በአረዛ አቅጣጫ ገፍቶ ወደ መንደፈራ ሰመሄድ ፈለገ እኛ ደግሞ በስተጀርባው ስለገባን ለቆ ሄደ ስለዚህ ሙልቂ ውስጥ በዚያን ጥልቀት ሌላ ጦር መቀመጥ አልነበረበትም ማንም ህሊና ያለው ሰው ያንን ትዕዛዝ አያስተላልፍም ብቻ ከእኛ ወገን በኩል የሆነ ምስጢራዊ ነገር አለን ነገር ግን የዚህ ምስጢር አፈትልኮ መውጣት ከማንና ከየት እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም ይህን ነገር ልንረዳው ወይም ልንፈታጡ አልቻልንም ቅንነት የጎደለው አመራር አሻጥርና ደባ አንዳለ ግን መገመት አትላለሁ የወቅቱን መንግሥት መጥላት ሌላ ነው ነገር ግን ለሀገር ሉአላዊነት የሚዋደቀውን ሕዝባዊ ሠራዊት አላግባብ ማስጨረስ ወንጀል ነው በማግሥቱ ተነስተን በአንድ ቀን ጉዞ መንደፈራ ለመግባት ግማሸ መንገድ ሲቀረን አደርን በማግሥቱ ተነሳንና አረ መንደፈራከመንደፈራ አመሻሸ ላይ አሥመራ ገባን አሥመራ እንደገባን አፋአበት ላይ ትልቅ ጦርነት ስለተጀመረ በአስቸኳይ በሌሊት ተነስታችሁ ወደ አፋአበት ሂዱ ተባልን በመጀመሪያ ደረጃ ይሄ ሠራዊት በጣም ደክሟል አንድ ቀን እንኳን መንፈሱን አዝናንቶና ደህና ምግብ በልቶ እንዲያድር የበላዮቻችን አልፈቀዱም ነዳጅ በቦቴ መጣልን ነዳጅ ሞላን ተወርዋሪ ስለሆንን ክፉ ነገር ከመድረሱ በፊት በትዕዛዙ መሠረት ጉዚችንን በጥዋት ቀጠልንና ከረን ገባን ከአንድ ሣምንት በፊት ግን በአቆርዳት ብሎክ በኩል ነበር የወጣነጡ የከረን ሕዝብ ሲያየን አንዴ ይሄ ጦር በዚህ በኩል ወጥቶ እንዴት ደግሞ በዚህኛው ዞሮ መጣ አለና «ከምሲን ብርጌድኔ የሚል ቅጽል ስም አወጣልን ከምሲን ነፋስ ነው ከምሲን በበረፃ በተለይም በኤርትራ በረሃዎች ያለ የአሸዋ ግድግዳ እየነዳ የሚፄድ አመጣጡ የማይታወቅ የአሸዋ ማዕበል ነው ሰንጥቅም ብዛት ያለው ዞው እንደማዕበል የሚፈስ አቅጣጫው አንዳንዴ የማይታወቅ የሰንጥቀም ትልቁ ግርማ ሞገሱ ያ ነበር ከዚያ ገሥግሰን ዕለቱኑ አፋበት ገባን አፋበት ገብተን ሁኔታውን ስንጠይቅ ሁሉም ነገር ሰላም ነው ምንም ነገር የለም ግደጁን አንዲወጣ የምንልከጡ ሠራዊት ለአንድ ቀን እንኳን መንፈሱን እንዲያዝናና ለመፍቀድ ከበላይ ፍላጎቱ አይታይም የዚህ ድምር ነበር መጨረሻ ላይ የሠራዊቱን ሞራል የጣለውና ር ለውድቀትም ያበቃን ወታደርን እንደ ሰው መሠረታዊ ፍላጎቱንና ሞራሉን ከጠበቁለት በውጊያም ላይ ሞራሉና ብርታቱ እንደ ብረት ይጠነክራል ይሄንን በተለያዩ የአመራርና የውጊያ መስመሮች ካገኘሁት ልምድ መናገር እችላለሁ በጥሩ ሁኔታ ወታደራቸውን መምራት የቻሉ አዛዥች ለእነሱም ለሚመሩትም ወታደር መልካም የሆነ ውጤት አስገኝተዋል ወታደሩን እንደ ሰው አድርገን መሠረታዊ ፍላጎቱን ጠብቀን ሞራሉንም አነቃቅተን ካልያዝነውና ካልመራነው ግን እንደ እንጨት ተሰባሪ ነው በወቅቱ የነበሩት አንዳንድ አለቆቻችን ሲያደርጉት የነበረው ሁሉ ከንግግራቸውና ከአድራጎታቸው ተምሮ የወታደሩን ሞራል የሚሰብርና ለውድቀት የሚዳርግ ነበር ያው እንግዲህ እንዳልኩት አፋአበት ገባን በሁለተኛው ቀን ከገዞ የመጣን ስለሆነ ውዛ በቦቴ አምጥተን እንደተለመደው የዘወትር ተግባራችን ብረትለበሶቻችንንና ታንኮቻችንን አጥበን ግሪዝ አደረግን ከዚያ በኋላ ጦሩ ገላውንና ልብሱን አፀዳ ወደ ጥገና የሚገቡትን አስገብተን ሥልጠና ጀመርን አረፍታችንንም ከዚያው አደረግንና እንደነገሩ ከአካባቢው ከሚገኝ ቁሣቁስ ጊዜያዊ መኖሪያችንን ሠራን የጥበቃ ቦታዎቻችንን ሁሉ አስተካከልን ሰንጥቅ በየደረሰበት ሁሉ በመጀመሪያ ቅድሚያ የሚሰጠው ለማብሰያ ቤቱ ለመኖሪያው ለንጽህና ቤቱና ለምሽጉ ነው በዚህ ዓይነት ሁኔታ እዚያው አፋበት ለረጅም ጊዜ ቀየን ተወርዋሪ እንደመሆናችን መጠን ጠቅላይ ሠፈራችንም አፋአበት ስለነበረ አዛዝፐች ከተለያዩ ግንባሮች ይመጣሉ ሁላችንም እርስ በርስ የምንተዋወቅ ስለሆነ እንደ ጓደኛ አንዳንድ ነገሮችን እያነሳን በግልጽ እንጫወታለን በአንድ ወቅት በዚያን ጊዜ ኮሎኔል በኋላ ግን ብርጋዴር ጀኔራል ኃይሉ ከበደ ቀደም ሲል በምሥራቅ ግንባር ኛ ሻለቃ ውስጥ አብረ ሠርተናል አሳቸው የአስተዳደር መኮንን እኔ ደግሞ ሻምበል አዛዥ ሆፔ ጅጅጋም ኛ ዱዱ ሩሩ መቹ ሜካናይዝድ ብርጌድ እነሱ ኛ ሻለቃ ሆነው እኔ ኛ ታንክ ሻለቃ ሆፔ የእስራኤሎች ረዳት ስለነበርኩኝ በረዳት አስተማሪነት ኛንም ሳስተምር እሳቸው የዘመቻ መኮንን ነበሩ ስለወቅቱ ሁኔታ አንድ ቀን ስንጫወት «ለመሆኑ ጠላት በሚቀጥለው ጊዜ የትኛውን ቦታ ወይንም ግንባር ያጠቃል ብለው ይገምታሉ። መኪናዎቻችን አኮ ያሉት አሥመራ ነው አልኳቸው ከዚያ ምንም አላልኩም ቀሪ ክፍሉን በሬዲዮ ጠራነው ለሰሜን ዕዝም መኪናዎቹ እንዲላኩልን ነገርን «ግድየለም ስለተነገራቸው ወደ እናንተ እየመጡ ነው» ተባልን እያንዳንዳችን እግራችን ተላልጧል በጣም ደክመናል አሁን ቀጥሎ ምን ይሆን እያልን ማሰብ ጀመርን ልክ ከዚህ ቀደም እንደሚደረገውና እንደፈራነው ለካ ጠላት ተሰነይን ደምስሷል እኛ ከአፋአበት ብንነሳ ለተሰነይ ውጊያ መድረስ ስለምንችል ሆን ተብሎ የተደረገ አሻጥር ነው ስለዚህ እኛ አንደዚህ ደክመንና እግራችን በተላላጠበት ወቅት ጠላት ተሰነይ ዜ ላይ ውጊያ ከፍቶ ተሳካለት ጥዋት መኪና ቀረበልን አሥመራ ገባን ከዚያ አቆርዳት ከአቆርዳት ተሰነይ እንድንሄድ ተደረገ ከቀኑ ሰዓት ላይ አቆርዳት ገባን ከአጭር ዝግጅት በኋላ በቀጥታ ወደ ባሬንቱ ተጓዝን ጠላት ሞኝ አልነበረም አድሜ ለነ አጅሬ ጥዋት እኛ መነቃነቅ ስንጀምር መረጃ ስለሚያገኝ እኛ ተሰነይ ገብተን ድምጥማጡን እንደምናጠፋው አስቀድሞ ያውቅ ነበር በማግሥቱ ተነስተን ጉኝ ከምትባል አንዲት ከፍታማ ቦታ ላይ ስንደርስ የበላይ አካል ተመለሱ የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈልን «ከምንመለስ ተሰነይ በጠላት መያዙ በሰፊው የተነዛ ስለሆነ ጠላቶቻችንም የሰሙ ስለሆነ እኛ ደግሞ መለቀቁንና የገባን መሆኑን ለማሳየት ባንቀመጥበትም ጠላት ሸሽቶ እንደሄደ ይታወቅ ለጠላት ስነልቦና የበላይነት አንስጠው» ብንልም ጀኔራል ረጋሣ ጅማ የበላይ ትዕዛዝ ነውና አይሆንም የሚል መልስ ሰጡን ብይ ፈደ መ ኀይለ ከ ዝቢ ደከ ፍፃ አው መ በዓ በጄ ሠ አ አወይቸ ማዩ ዓው መ ህዝ ሃሃ መ ለዘ ሄቬ በ ዓም ሠንጥቅ ሜካናይዝድ ብርጌድ ከርከበት ላይ ሲቋቋም የመጀመሪያ መምሪያ ለጦሩ ሲሰጥ ሙፌዴዴ ጹጮሙው ቸቸ ኣሩ ስልጠና በአቆርዳትና ከብረትለበስ የመገልበጥ አደጋ የመጨረሻ ጠርዙ ባሬንቱ ስለሆነ አኔ የምመራው ጦር በተጠባባቂነት ወደ አፍአበትና ወደ ባሬንቱ ላለው ጦር ለመወርወር ምቹ ቦታ ወደ ሆነው አቆርዳት ገባን ከግዳጅ መልስ ወደ አቆርዳትና ወደ አፍአበት ስንመለስ ድል እያደረግን በልበ ሙሉነትና የተበላሸውን ሁሉ እያቃናን በደስታ ነበር የምንመለሰው ሰንጥቅ የሚያጋጥመውን ወታደራዊ ግዳጅ በጀግንነትና በጥንካሬ ሲወጣ የቆየ ጦር ነው አቁርዳት ላይ መልሰን እንድንሰባሰብ ከተደረገ በቷላ ትኩረታችንን ወደ ሥልጠና አደረግን የአቆርዳቱ ሥልጠና የነፍስወከፍ መሣሪያችን ውጤታማ በሚሆንበትና በሚጠናከርበት ሁኔታ ላይ አተኮረ በእርግጥም ስለ መሣሪያ የነበረን ትምህርትና በየጊዜው ያደረግነው ልምምድ ጠንካራ ቢሆንም ሠራዊቱ ሳያልም በጠላት ላይ እንኳን ቢተኩስ የበለጠ ውጤት የሚያገኝበት ስለሆነ መሣሪያችንን ከአስተካክልን በኋላ ሠራዊቱ በቁም እንዲተኩስ ተምህርት መስጠት ጀመርን ይህንን የተመለከትኩት ብዙ ጊዜ ሰንጥቅ ውስጥ ተወርውረን በምንሄድበት ጊዜ በአብዛኛው ጥይቱ ወደ ሰማይ የሚሄድ ስለሆነ አእየፄዳችሁ በትከሻ ቁጥጥር ተኩሰ አስፈላጊ ሲሆን ደግሞ ቆማችሁ ተኩሱኔ የሚል ሥልጠና ስለነበረ ያንን መመሪያ ከሰጠን በኋላ በጠላት ላይ ጥሩ ጥሩ ወጤቶችን አስገኝቶልናል አሁን ደግሞ መሣሪያን አስተካክሎ ይህንን መከተሉ አስፈላጊ ስለነበረ ያንን ሥልጠና በሰፊው ተያያዝነው የካቲት ቀን ዓም ሁለት ቃፒሺ ጦሮች ወደ ባሬንቱ አቅጣጫ በተከረሪት ወደ ከርከበት ላክሁ የጠላት እንቅስቃሴ በዚያ አካባቢ ይኖራል የሚል ግምት ነበረን ሁለቱም ቃፒ ጦሮች ፌዴ ኢሔጧጤዱ በተባለው አቅጣጫ ከወጡ በኋላ ምንም ዓይነት የጠላት እንቅስቃሴ አላገኙም በትልቁ ሬዲዮ ሊገናኙ ስለማይችሉ ባሬንቱ አቅጣጫ ሣርቃት ወደሚባል ጉብታማ ሥፍራ ወጥቼ በቀላሉ ላገኛቸው ስለምችል ወደዚያው ስሄድ አንድ የሜዳ ፍየል መሃል መንገድ ላይ ገብቶ ይቀማል ያ የወጣትነት የአደን ስሜቴ ተቀሰቀሰና ብረት ለበሱ አየፄደ ስተኩስ ሳትኩት ሾፌሩን አቁምልኝ አልኩና እንደገና ብተኩስ አሁንም ደግሜ ሳትኩት ይባስ አለና ወደ ኋላችን ዞሮ አቅጣጫውን ወደ አቆርዳት አድርጎ መሐል መንገዱ ላይ ቆመ አሁንም መልሼ እንዳልስተው ሰጋሁና ወደ ኋላ ሰፋ አድርገን ሄደን ወደ ባሬንቱ አቅጣጫ አስገባነው በዚህ ጊዜ ከመንገዱ ሳይወጣ መንገዱን ተከትሎ የተወሰነ ርቀት ከሄደ በኋላ ቆመ እኛም ቆመን ተኮስን ወርቹ ላይ ያለምኩት ዝቅ ብሎ እግሩ ላይ አረፈ ከመንገዱ ወጥቶ ሳሩ ላይ እያነከሰ ሲፄድ ጥይት ማበላሸት የለብንም አልንና በብረት ለበሱ ተከተልነው ቦታው ቀደም ሲል በጎርፍ የጎደጎደና ሳር የበቀለበት መሬት ስለሆነ ፍጥነታችንን ጨምረን ስንከተለው ሳናስበው ብረት ለበሱ ሳሩ ከከለለው ጉድጓድ ውስጥ ገባ ብረት ለበሱ ባለ ጎማ ነው የመጀመሪያው ጎማ እንደገባ ወደ ላይ ወረዐወረን ሁለተኛው ሲከተል በብረትለበሱ ላይ ተከሰከስን ትዝ ይለኛል ሻለቃ አድማሱ መላኩ የኔ ዘመቻ ረዳት የነበሩ ሲሆን የታችኛው ጥርሳቸውና ድዳቸው ተጎዳ እኔ ደግሞ በጀርባዬ ብረትለበሱ ላይ ወደቅሁ የሬዲዮ ኦኘሬተሩ ደግሞ ሜዳ ላይ ወርዶ ተፈጠፈጠ ከዚያ በኋላ ያ አውሬ የት እንደገባ ልናየው አልቻልንም አኔ ህሊናዬን ትንሸ ስቼ ስለነበረ መኮንኖች አንስተው አቀርዳት ሆስፒታል አስገቡኝ እንደተነገረኝ ወደ ደቂቃ ከቆየሁ በኋላ አራሴን አወቅሁ በጀርባዬይ በኩል የተቀጠቀጠው ቦታ ስር ጩዲፍክህዱስቸዱ ፍቴ ሬር ተበጥሶ ደሙ በጀርባዬ ላይ ተጠራቀመ የጀርባ አከርካሪዬ በሚሊም ሳይነካ መቅረቱ እንጂ ከፍ ያለ ቢሆን ኖሮ ሽባ ፓራላይዝድ ልሆን እችል ነበር ያ የተበጠሰው ስር በአካሌ ውስጥ በፈጠረው የደም መጠራቀም ምክንያት በሃይል የማቃጠል ስሜት ተሰማኝ መኮንኖቹ ሄሊኮኘተር ጠየቁና በቃሬዛ ከሆስፒታሉ አውጥተው ወደ አውሮኘላን ማረፊያ ሊወስዱኝ አምቡላንስ ውስጥ ስገባ ከሆስፒታሉ ውጭ የአቆርዳት ህዝብ በብዛት ግቢውን ሞልቶታል የአቆርዳት ህዝብ በተለያዩ ጊዜያት በዚያ አካባቢ በሠራሁባቸው ወቅቶች በሚገባ ያውቀኛል ሰንጥቅ ለአቆርዳት ህዝብ ባለውለታው ነው እስከ ቀይ ኮከብ ድረስ መብራትም የውሃ ጀኔሬተርምየማይሠራ ስለነበር ውዛ በቦቴ በየእለቱ እንደየአቅሙ ከጣሳ ጀምሮ እስከ ጀሪካንና በርሜል ድረስ እናድል ነበርአንዳንድ ችግረኞች በወባ ሲያዙና ህክምና ሲያስፈልጋቸው በሠራዊቱ ክሊኒክ ውስጥ በነጻ እንዲታከሙ እናደርግ ነበር ህዝባዊ ሥራ መሥራት ያለብን ስለሆነ በተለይም ለእኔ አምነቴም ስለነበረ ህዝቡን እንረዳ ነበር ጀብሃ ያፈራረሰውን የአርሻ መሬት እንደገና እንዲለማ ያደረገ ሠራዊት ነው ትራክተሮቹንና የውሃ ፓምፖችን ጦሩ ጠግኖ ሥራ ላይ አንዲውሉ አድርጓል ጦሩ የምርቱን ውጤት ከቀበሌው የሚገዛው በገንዘቡ ነው እንጂ ድጋፍ አድርጌያለሁ በሚል በነጻ ለመጠቀም ዛሳቡም ፍላጎቱም አልነበረውም በዚያን ወቅት ሻዕቢያ በሠራዊቱ ላይ ከፍተኛ የጥላቻ ኘሮፓጋንዳና ቅስቀሳ ሲያካሂድ ድርቅ በተነሳበት ወቅት ሠራዊቱ ከራሱ ቁርስና ምሳ እየቀነሰ ብስኩቱን በሶውን ወተቱንና የመሳሰለውን ሁሉ በሁለትና በሶስት ኡራል መኪና እየጫነ ለአቆርዳት ህዝብ ይልክ ነበር ይህንን ዛሬ ውስጡ ሄዶ የሚያናግረው ሰው ቢገኝ የአቆርዳት ህዝብ አውነቱን ይመሰክራል ዴዴ ው መ ሥኡሥጨጨሬሬሬሙሬጮ ረ ጋ ኤ ጆ እንኳን ሰው ግንቡና ዛፎቹ አናጋሪ ቢያገኙ ዛሬም የምስክርነት ቃላቸውን ይሰጣሉ ጠላት ግን ሠራዊቱ ህዝብን እንደሚዘርፍ ያስወራል እኛ በጠላትነት የተፈረጅነው ለህዝብ እናደርግ የነበረውን ያህል ዛሬ ሻዕቢያ ያደርገዋል የሚል ግምት የለኝም በከተማው ውስጥ የነበረው ተሽከርካሪ የአስተዳዳሪው የግራዝማች ኢጀል አንድ ላንድሮቨር ብቻ ነው በሌሊት በሰው ላይ ድንገተኛ አደጋ ቢከሰት እንኳን ወደ ሆስፒታል የሚወስድ አምቡላንስ ስለሌለ የጦሩ አምቡላንስ በቋሚነት ለዚህ ተግባር ተመድቦ ነበር እንግዲህ ያ ሁሉ ህዝብ በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተሰበሰበው ሠራዊቱን የምመራው እኔ ስለነበርኩ ያንን እንደ ውለታ በማየት ነው የተሰበሰበው ህዝብ አልቅሶ ሲሸኘኝና የህዝቡን ጭንቀት ስመለከት «አይዚችሁ ተርፌያለሁ በቅርብ ቀንም ተመልሼ እመጣለሁና አታስቡ በማለት በልቤ እያዘንኩና ህዝቡ ሰእኔ የነበረው ፍቅር እያስገረመኝ ብዙ ነገሮችን በሀሳቤ እንዳውጠነጥን አደረገኝ በነገራችን ላይ ግራዝማች ኢጀል የቤኒአሚር ተወላጅና በአንድ ወቅት ናቅፋ ላይ መምህር ሆነው ሰርተዋል ግራዝማች ኢጀል ጨዋ ቀልደኛና ኢትዮጵያ ሃገራቸውን ከልብ የሚወዱና ሃቀኛ ሰው ናቸው በባሬንቱ መከላከል ወቅት የባሬንቱ አስተዳዳሪ ሲሆኑ የኩናማ ብሄረሰብን አደራጅተው ከጦሩ ጎን አሰልፈዋል ግራዝማች እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ስለነበሩ ሻዕቢያ ኤርትራን ሲይዝ እርሳቸውንና መሰል ኢትዮጵያውያንን እስር ቤት ወረወራቸው ግራዝማች ግን ቃል ኪዳናቸውን እንደጠበቁ እዚያው በአስር ቤት መስዋዕት የሆኑ ጀግና ናቸውወ ሩሩ ቫት ይዬ ቸፍ መ አሥመራ እንደደረስኩ ገጀረት ሆስፒታል ገባሁ ገጀረት ሆስፒታል ውስጥ ከተለያዩ የጦር ሜዳዎች የመጡ ብዙ ቁስለኞች ገብተዋል በእኔ ላይ የደረሰው አደጋ ከሌሎቹ ቁስለኞች ጋር ሲነፃፀር በጣም ቀላል ነው ዶክተሩ ብጀ ታደሰ መልካ የጀመሩዋቸውን የቀዶ ጥገና ህክምናዎች ካጠናቀቁ በኋላ እኔ እንድገባ አደረጉ የሰመመን መድሐኒት ከሠጡኝ በኃላ ያን በአካሌ ውስጥ ተጠራቅሞ የነበረውን ደም አስወገዱልኝና በጀርባዬ እንድተኛ ተደረገ የቃኘው ሆስፒታል ኃላፊ በሁለተኛው ቀን ሲገቡ አዩኝ ዶር ደስታ ይባላሉ ከፓሪስ የተመለሱት በራሳቸው ፈቃድ ነው አጅሬዎች ስለአልተመቿቸው አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ተመልሰው ፄዱ ዶር ደስታ ከገጀረት ወደ ቃኘው ሆስፒታል እንድዛወር አደረገ እኔ ያን ጊዜ ሌተና ኮሎኔል ነበርኩ ቃኘው ሆስፒታል ውስጥ ከፍተኛ መኮንኖች በተለይም ጀኔራሎች የሚተኙባቸው የተወሰኑ ክፍሎች አሉ ከእነዚያ ክፍሎች በአንደኛው ክፍል እንድተኛ ካደረጉ በኋላ ጥዋት ቀንና ማታ ይከታተሉኝ ነበር ቁስሉ ከአንድ ሳምንት በኋላ ውስጡ ማዣት ስለጀመረ እንደገና የቀዶ ጥገና ህክምና ተደረገልኝና አስፈላጊዎቹ መድዛኒቶች ታዘዙልኝ የሐኪም ዕረፍት ሐኪም ለአንድ ወር ሳላቋርጥ ፊዚዮቴራፒ እንዳደርግ ነበር ያዘዘኝ ለጥቂት ቀናት ያህል ናዝሬት ከቤተሰቤ ጋር ካረፍኩ በኋላ አዲስ አበባ ፄድኩና ምድር ጦር ሪፖርት አደረግሁ ለሆስፒታሉም የሕክምና ሰነዶቼን አቀረብኩ ዶክተር ጋጋም መድሐኒት አዘዙልኝና በየቀኑ ለአንድ ወር ፊዚዮቴራፒ አንድወስድና ለውጥ ካልተገኘም ወደ ውጭ ሀገር ሄጄ እንደምታከም ገለጽልኝ ው ዴ ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact