Detecting...
Please whitelist dirzon to continue.
እኔም ወደዚያው እየሄድሁ ነው። ረጋ በዬ ደግሞ። ሰሎሜ ደግሞ የጥፋተኝነት ስሜት ኢያሠቃያት ነው። እሱም አጣርቶ ጉዩን እንደሚከታተል ነው የነገራት። እሱም ከዚህ ቡድን አመራሮች ጋር አንዳንድ ግጭት ሳይኖረው እንዳልቀረና ከቡድኑ ለመልቀቅና ወደ ውጪ አገር ለመሄድ እያቀደ ከዚያ ጋር ባልተያያዘ ምክንያት ሶፊያን ለማስገደል በተከፈላቸው ገንዘብ ጦስ ነው ሁለቱንም ሊገድሱዋቸው የሞከሩት ብሎ አስረድቶአቸዋል። ባልቻም እመጣለሁ ብሎኝ እየጠበቅሁት ነው አሌ። ዛሬ ራት አዘጋጅተው ዐብረው ሲጫወቱ ሊያመሹ ነው ያቀዱት። አይ ብቻሽንማ ጥሩ አይደለም ቀኑም እኮ እየመሸ ነው። ብለው ካፋቸው ሳይጨርሱ መሬት ላይ ቁጭ ብሎ ጌም ሲጫወት የነበረው የሰባት አመቱ ያክስቷ ልጅ እስክንድር እኔ ዐብሬሽ እሄዳለሁ ብሎ ተስፈንጥሮ ተነሥቶ እላዩዋ ላይ ተጠመጠመ። ሰፈሩ ንጹሕ አረንጓዴና እምር ያለ ነው የሚመስለው። ይህ ሶለን ኢትዮጵያ ስሄድ የሰጠኝ ስጦታ ነው። ብላ እጂ ላይ አስቀመጠችው። ሰወ እኮ ስለ ሞቱ ብቻ ሳይሆን ስላሟሟቱም የሚጨነቅ ፍጡር ነው። ኀዘኑዋም የተወሰነ የቀነሰላት መስሎአታል በሰማችው ነገር። እንዲያው ግን የሰው ሕይወት እንዴት ውስብስብ ነው። ጀርመን ተወልዳ ግሪክ አድጋ አሜሪካ ተምራ አሁን ደግሞ ኢትዮጵያ ልትሄድ ስለሆነ ዕቃዋን ሁሉ መልክ መልክ እያስያዘች ነው። የተወሰኑ ዕቃዎቿን መርጣ የፅቃ ማስቀመጫ ክፍል በመከራየት እዚያ አድርጋ ለመሄድ ነው ያሰበችው። ሶፊያ ለሰሎሜ የነገረቻት ታሪክ ከሶለን ጋር በነበራቸው ግንኙነት የተፈጠረውን ሁኔታ ለማስረዳት የሚያስችላትን ብቻ ነው። እየደበዘዘ ሲያሻው ደግሞ እየደመቀ። ሌሎቹ ሁለቱ ልጆቿ ካባታቸውና ካያቶቻቸው ጋር ወደ ደብረማርቆስና ባሕርዳር ለአንድ ሳምንት ቆይታ ከሁለት ቀን በፊት ስለሄዱ በአንድ በኩል ትንሽ እፎይ ብላ ነው የሰነበተችው። ለአንድ ሰዓት ያሀል ከዋኙ በኋላ ሳውና ባዝ ወስዳ ማሳጅ አድርጋ ስለነበር ነው መሰል የድካም ስሜት ቢኖራትም እንኳ ለራት ሲወጡ የረጋ ሰውነቷ ሁሉ ተፍታቶአል። ከዚህ ዐይነቱ ጥሩ ቀን በኋላ ግን የማትችለው ነገር አይኖርም። ሣራ አዲስ አበባ ውስጥ ያሉትን የአእምሮ ህክምና አገልግሎቶች ሁሉ ጐብኝታለች። በተለይ ከሕፃናትና ወጣቶች አንጻር ያለዉን ከፍተኛ ጉድለት ለመቅረፍ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለባት እያሰበች ነው። ምክንያቱም ምንተስኖትም ሆነ የሱ ቤተ ሰቦች በጥብቅ የሚቃወሙት ሐሳብ እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው።
ሶለን ደኅና አይደለም እንዴ። ዐሥራ አንድ ሰዓት ሲሆን ሶስናን ከትምህርት ቤት ሊቀበል ሄደ። ምክንያቱም እሱ ዐዋቂ ሰው ነው እሷ ደግሞ ልጅ። እዚህ ብዙ ጊዜ ሠሩ እንዴ እርይ። በጣም ረጂም ጊዜ ነው ልጄ ምነው ውጪ አገር ነው እንዴ የምትኖረው ይህንን ሁሉ ዘመን ሳትተያዩ። እም አይ አባቴ ሌላ ቦታ ነው ያለው። አይ አሁን እንኳ አንድ ሦስት ዓመት ሆነ መሰል አይቼያቸውም አላውቅ ። ሊጠይቃቸው ካዲሳባ መጥቶ ግን ያው ምንም ስለማያውቅ የት እንዳለች እዚህ ቴሌ ትሠራ ነበር ስላለኝ አንተ መቼም የማታውቀው ሰው የለም ብዬ ነው። እዚህ ያለው ነገር ምንም ፍሬ አልነበረውምና በቃ እዚሁ አድሬ አዲሳባ ነገ ልመለስ ነበር። ሁሉም እየተንጫጩ ከቆሙበት ቤት ፊት ለፊት ሦስት ቤት ርቆ ያለውን ቤት እየጠቆሙ እዛ በሩ ላይ ጣሳ የተሰቀለበት ቤት ግቢያቸው ውስጥ ትልቁ ዛፍ ያለበት እያሉ ወደ ቤቱ አመለከቱ። በዚህ መሃል አንድ ወደ ሰባት ዓመት የሚጠጋው ልጅ የኛ ቤት ነው የኛ ቤት ነው እያለ ደስታና ኩራት በተቀላቀለው ሰሜት ከልጆቹ መሃል ተጋፍቶ ወደ ፊት ቀረበ። ይህ ሁሉ ሲሆን ግራ የገባቸው ሕፃናት ነገሩን እንደ ጉድ እያዩ ከበዋቸው ይቅበጠበጣለ ወይዘሮ አሰለፈችን ጠርቶ የመጣው ልጅ ግን አሁንም ወደ ቤት እየበረረ ሄደ። ራሳቸውን ለመቆጣጠር ብዙም ጊዜ የማይወስድባቸው ወይዘሮ ብሪቱ ክረ በቃ በቃ ዛሬ የፌሽቷ ቀን ነው። አንተ ሰው ታስከፍላለህ እንዴ ግን። ደግሞ ትንሽ ልጅ እኮ አይከፍልም። ልጅ አለህ እንዴ። እዚያ ብዙ ሰው አለ እንዴ። ውድ ስለሆነ በቃ ሥጋ ብቻ ነበር የተገዛው እኛ ቤት። ከዚያም አንድ ተለቅ ያለ ሱቅ ገብተው ሁለት ሣጥን ለስላሳና አንድ ሣጥን አምቦ ውሃ ገዝተው ወደ ቤት ሄዱ። አለችው አንድ ቀሚስ ያደረገ የሚያለቅስ ትንሽ ልጅ ዕድጫዋ ዐሥር ዓመት አካባቢ የሚሆናት ልጅ ታቅፋው። አንድ ጊዜ መናገሯ የሚበቃው መዐዛ እንዴ እናንተን እኮ ነው። ውጪ አገር የስመኝ መሥሪያ ቤት ሰዎች ወስደውታል ስላሉን በቃ ተስፋ ቆረጥን። እንዴ እኔ ብቻዬን አንድ አልጋ ይደርሰኛል እንዴ። መላኩም ከመሄዱ በፊት ለልጆቹ ሁለት ሁለት መቶ ብር ላክስቱ ልጆች አንድ አንድ ሺህ ብር ላክስቱ ደግሞ ሦስት ሺህ ብር ሰጣቸው። ከዚያም ትንሽ ዝም ካሉ በኋላ እንደ ምንም ሌላ ጨዋታ አምጥተው ትንሽ ተሣሥቀው ተለያዩ። ምንም። ትንሽ የለም ትልቅ የለም። መላኩ ምንም ዕዳ የለበትም ይሄ ሁሉ ሰው እየተንጋጋ እዚህ። አንድ ቤተሰብ አንድ ልጅ መለሠጥ። አንዴ ሲጮኸ ነበር ስልኩን ያነሣው ማርቆስ አጅሬው ሰው ያስባል አትልም እንዴ በዚያው እልም ይባላል እንዴ እኔ ኮ በቃ ልመጣ ሁሉ ነበር በጣም ነው የተጨነቅሁት ደግሞ ስልክህንም ሆቴልህ የረሳኸውም መሰለኝ እሺ እስኪ ንገረኝ ሣ አለ ወቀሣውንም የጉዞውንም ውጤት ለማወቅ ያለውን መቅለብለብ በሚገልጽ ድምፅ ማርክ ማርክ በጣም ሶሪ ስልኬን መኪናዬ ውስጥ ረስቼው በቃ ምንም ልቤ ሁሉ ጠፍቶ ነበር ገምት የሚገርም ነው አገኘኋቸው ገና አሁን ነው የተለያየነው ልነግርህ አልችልም በቃ ቁጭ ብለን የምናወራው ነው እንጂ አሁን በስልክ የሚያልቅ አይደለም። ቆየህ እንዴ እዚህ አለው አሁንም ዐይኑን ከሱ ላይ ሳይነቅል አይ ሦስት ወሬ ነው። አለ መላኩ አሁንም ትውውቁን እያጠናከረ የዚሁ አገር ልጅ ነው። ለምን እንደሆነ አላውቅም ብዙም ጊዜ ያለኝ አይመስለኝም አይ ዶኖ በቃ ተይው አሱን አሁን ለማንኛውም ፐርሰናል የሚለው ፋይል ውስጥ ግቢና ሁለት ጽሑፎች አሉ አገኘሻቸው። አሁንም ሆስፒታል ነው እንዴ። ቆይ አንድ ጊዜ ብላ ፊቱን አዙሮ ወደ ግድግዳው ተኝቶ ያለውን ሶለንን ሶለን ሶለን ሶፊያ ነች ሶፊያ ስትለው ከየት እንዳገኘው በማይታወቅ ዐቅም ብድግ ብሎ እም ምን ደወለች እስኪ እያለ እጁን ዘረጋ ስልኩን ሊቀበላት። ግራ እጂ ላይ ያለው ቁስለት ትንሽ ቢሰማትም ላለፈው አንድ ሳምንት ትንሽ ነድታ ስላየችው ብዙም አላስጨነቃትም። ቆንጆና የቤት ልጅ ዶክተር አግኝቶ ልቡ ስለሰከረ አገር ቤት መጥቶ ሊያገባት የነበረችውን የረጅም ጊዜ ዕጮኛውን የሌለች ያህል ዘጋት። ይላል መላኩ። ምንተስኖት ከመጣ ዝም ብሎ የቆየው ማርቆስም ራት ላይ ትንሽ ተጫውቶ ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ መላኩ ቤት ሊያድሩ ሄዱ። አለ መላኩ። በርግጥ እነሣራን አንድ ሁለት ጊዜ ራት ጋብዞአቸዋል። ወደ ዐሥራ አንድ ሰዓት ላይ አዲሳባ ሲደርሱ መዐዛ ስልክ ደውሳላለት ከስቴዲየም አካባቢ ሄዶ ተቀብሏቸው ወደ ቤት ሄዱ። በቃ በጣም ትልቅ ቢዝነስ ኖሮኝ ብዙ ሰው ስረዳ ውጭ አገር ስሄድ ምናምን። ከዚያ በቃ ያለፈው ሁለት ዓመት የኖርኩት ሳይሆን የቀን ቅዥት ውስጥ የነበርኩበት ጊዜ ነበር። ከጓሮ ላለው ቤት አንድ አምሳ ሺ ብር ቢፈድ ትልቁን ቤት ደግሞ አንድ ሃያ ሺ ብር አውጥተን ብናሳድሰው አይበቃም። ከዚያ በኋላ ማንም ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። ስለ አደጋውም ሆነ ከዚያ ጋር ስለተያያዘው ጉዳይ ገና ምንም አላወሩም ድንገት ሶፊያ በመጣችበት ቀን ሶለን ስላረፈ። ትምህርት ቤት ሲዘጋ ሰሎሜና ሶለን እሱ ጋ እየሄዱ ብዙ ጊዜ ያሳልፉ ነበር። አስተናጋጁ እዚህ ቤት እጅግ ብዙ ጊዜ ከቆዩት ጥቂት ሰዎች መካከል አንዱ ነው። ያው ጊዜ ይወስዳል። ለካ አባቴ ከዚህ በፊት ሁለት ጊዜ አግብቶ የፈታና ሦስት ልጆች የነበሩት ሰው ነው። በዚህ ጊዜ እኔ የአራት ወይ የአምስት ዓመት ልጅ ነበርኩ። በዚህ ጊዜ የአስር ዓመት ልጅ ነበርኩ። አንድ ሁለት ጊዜ መጥቶ ነበር ግን ለምን እንደሆነ አላውቅም እሱ ሲመጣ የቀጣሁት ስለሚመስለኝ ይሁን ናፍቆቱ ሆድ ስለሚያስብሰኝ እንደገናም ቀርቦ መለየቱን ስለፈራሁ በቃ አልቀርበውም ወይም አንድ ቀን እንዲህ ካየሁት በሁዋላ ዐይኑን ማየትም እንቢ እላለሁ ሌሊት ደግሞ ሳለቅስ አድራለሁ። አለች ሰሎሜ አሁንም አይኖቿ ሶፊያ ላይ እንደተሰፉ በሳምንቱ እናቴ ቤት ትልቅ የቤተ ሰብ ስብሰባ ተደረገ እናቴም የሕመሟን ጉዳይ ነግራቸው ሁሉም ሰው በጣም አዘነ። በቃ እግዜር ቤተ ሰብ ሰጠኝ ሁለት ወር እቆያለሁ ብዬ የሄድኩት ሳላስበው ብዙ ጊዜ ቆየሁ። ብዙም ሰው አልነበረም። ዐላማችን አንድ ሁለት አመት እዚያ ከሠራን በኋላ እዚህ ያለው ነገር ምንም የማይሻሻል ከሆነ ትንሽ ገንዘብ አጠራቅመን ኢትዮጵያ ገብተን ለመኖር ነበር። በቃ አለ አይደል። ሣራና መላኩ አሜሪካ ከመሄደ በፊት ስለነበራቸው መልካም ትዝታ እያወሩ ሁለቱም ርቧቸው ስለነበር ወደ አንድ የሚያውቁት ፒዛ ቤት ሄዱ።